በሀገሪቱ የተጀመረው የብልፅግና ጉዞ እውን እንዲሆንና ዘለቄታ ያለው ሠላም እንዲረጋገጥ የወጣቶች ሚና የላቀ ሊሆን እንደሚገባ ተጠቆመ
“እኔ ለሀገሬ የሠላም ዘብ ነኝ” በሚል መሪ ቃል ከተማ አቀፍ የወጣቶች የውይይት መድረክ በአርባምንጭ ከተማ አየተካሄደ ይገኛል።
በውይይት መድረኩ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የጋሞ ዞን አስተዳደር ተወካይ እና የዞኑ ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ሀላፊ አቶ ማዜ ሸቀኔ ፤ በሀገሪቱ የተጀመረው የብልጽግና ጉዞ እውን እንዲሆንና ዘለቄታ ያለው ሠላም ሰፍኖ ዜጎች በሀገራቸው ተረጋግተው መኖር እንዲችሉ ለማስቻል የወጣቱ ሚና የላቀ ሊሆን እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በዞኑ እየተስተዋለ ያለውን የወጣቶች ሥራ አጥነት ችግር ከመቅረፍ አኳያም ወጣቱን በተለያዩ የሥራ መስኮች በማሰማራት ራሱንና ሀገሪቱን በሚጠቅም መልኩ ሥራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በውይይት መድረክ በርካታ የአርባምንጭ ከተማ ወጣቶች እየተሳተፉ ይገኛሉ ።
ዘጋቢ: እንጃ ገልስሞ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በወሊድ ምክንያት የሚሞቱ እናቶችን ቁጥር ለመቀነስ የተጀመሩ ስራዎች አበረታች ውጤት እያስመዘገቡ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ
የፃማኮ ብሄረሰብ የዘመን መለወጫ የ”ባርባይሳ” በዓል የህብረ ብሄራዊ አንድነት መገለጫ፣ የሰላምና የመተሳሰብ ምልክትነቱን በማግዘፍ ለዓለም አደባባይ ማብቃት ይገባል ሲሉ የክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ገለጹ
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ