ሀዋሳ፡ የካቲት 07/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ “በባህል እሴቶች፣ ሀገር በቀል ዕውቀት ብዘሃ ባህል አብሮነት፣ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችና አሉታዊ መጤ ባህሎች” ዙሪያ ለዞን ባህል ቱሪዝምና ሰፖርት መምሪያ አመራሮች፣ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት የተዘጋጀ የስልጠና መድረክ በኮንታ ዞን እየተካሄደ ይገኛል።
የክልሉ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊና ባህል ቱሪዝም ዘርፍ ኃላፊ አቶ አክሊሉ ለማ በመክፈቻ ንግግራቸው ስልጠናው ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚሰጥ ሲሆን የባህል ተምሳሌት እና አገር በቀል ዕውቀት ከፍ ለማድረግ እንደዚህም ጎጂ ባህላዊ ድርጊቶችንና መጤ ጎጂ ባህሎችን ለማስቀረት ባለድርሻ አካላትን ለማነቃቃትና በቅርበት ለመስራት ትኩረት የተደረገበት ስልጠና መሆኑን ተናግረዋል።
ዘጋቢ: ፋሲካ ሙሉጌታ – ከዋካ ጣቢያችን
More Stories
ታላቁ የህዳሴ ግድብ ተጠናቆ መመረቅን ምክንያት በማድረግ የይርጋጨፌ ወረዳ እና ከተማ አስተዳደር በጋራ በመሆን የድጋፍ ሰልፍ አካሄዱ
ሙያዊ ስነ-ምግባር የተላበሰ አገልግሎት በመስጠት የተገልጋዩን እርካታ ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ ተገለፀ
የካፋ ዞን ጤና መምሪያ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2018 ዕቅድ ዝግጅት ላይ ውይይት እያካሄደ ነው