ሀዋሳ፡ የካቲት 07/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ “በባህል እሴቶች፣ ሀገር በቀል ዕውቀት ብዘሃ ባህል አብሮነት፣ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችና አሉታዊ መጤ ባህሎች” ዙሪያ ለዞን ባህል ቱሪዝምና ሰፖርት መምሪያ አመራሮች፣ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት የተዘጋጀ የስልጠና መድረክ በኮንታ ዞን እየተካሄደ ይገኛል።
የክልሉ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊና ባህል ቱሪዝም ዘርፍ ኃላፊ አቶ አክሊሉ ለማ በመክፈቻ ንግግራቸው ስልጠናው ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚሰጥ ሲሆን የባህል ተምሳሌት እና አገር በቀል ዕውቀት ከፍ ለማድረግ እንደዚህም ጎጂ ባህላዊ ድርጊቶችንና መጤ ጎጂ ባህሎችን ለማስቀረት ባለድርሻ አካላትን ለማነቃቃትና በቅርበት ለመስራት ትኩረት የተደረገበት ስልጠና መሆኑን ተናግረዋል።
ዘጋቢ: ፋሲካ ሙሉጌታ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ምክንያት በማድረግ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች የምረጡን ቅስቀሳና ድጋፍ ሰልፍ በኣሪ ዞን ጋዘር ከተማ አካሄዱ
በጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳ እና በላሃ ከተማ አስተዳደር የብልጽግና ፓርቲ የማጠቃለያ ሕዝባዊ የምርጫ ቅስቀሳ ፕሮግራም ተካሄደ
የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምጽ መስጫ ቀን 7 ቀናት ብቻ ቀርተውታል