የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበራዊ ክላስተር የመንግስት ሰራተኞች ስልጠና በወራቤ ከተማ ተጀምሯል።
ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ ሀላፊ አቶ ገብሬ ጋጌ፤ ባለፉት አምስት አመታት በኢትዮጵያ በርካታ ውጣ ውረዶች ቢኖሩም ከዚሁ ጎን ለጎን በበርካታ ዘርፎች ዓለም አቀፍ ዕውቅናን ያገኙ ውጤቶች መመዝገባቸውን አመልክተዋል።
የመሰረተ ልማት ግንባታዎች፣ ትላልቅ ሜጋ ፕሮጀክቶች፣ የስንዴና የልማት ትሩፋትና መሠል ዘርፎች በውጤታማነት የዘለቁ ናቸው ብለዋል አቶ ገብሬ።
ከዕዳ ወደ ምንዳ በሚል ርዕስ እየተሰጠ ያለው ስልጠና በሁሉም አካባቢዎች በየደረጃው እየተሰጠ ስለመሆኑ ጠቁመው ሰላምና ልማት እንዲሁም መልካም አስተዳደር የስልጠናው ማጠንጠኛ ነጥቦች ናቸው ብለዋል።
የሀገሪቱን መንግስት ፖሊሲና ስትራቴጂ በአግባቡ የተረዳ የመንግስት ሰራተኛ መፍጠርና ህብረተሰቡን በአግባቡ እንዲያገለግሉ ማስቻል ደግሞ የስልጠናው ግብ ነው ብለዋል።
በሁሉም ዘርፎች የተሰማሩ ዜጎች የግልና የጋራ ግዴታቸውን በመወጣት ለሃገራዊ ብልፅግና የበኩላቸውን እንዲወጡም አቶ ገብሬ ጥሪ አቅርበዋል።
ለስልጠናው የተዘጋጁ ጥናታዊ ሰነዶች ቀርበው ሰፊ ውይይት እንደሚደረግባቸው ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
በዚህ ስልጠና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መቀመጫቸውን በወራቤ ከተማ ያደረጉ የትምህርት፣ የጤና፣ የፐብሊክ ሰርቪስ፣ የሴቶችና ህፃናት እንዲሁም የሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ቢሮ የስራ ሀላፊዎችና ሰራተኞች እየተሳተፉ ነው።
ዘጋቢ፡ ጀማል የሱፍ

More Stories
በጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳ ከ22 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ለሚገነባው የእንስሳት ግብይት ማዕከል ግንባታ የሳይት ርክክብ ተደረገ
የሀገራችንን ብልፅግና እውን ለማድረግ በበቂ ዕውቀትና ክህሎት የታነፁ ምሁራንን በማፍራት የተሻለ ትውልድ መቅረጽ ቁልፍ ተግባር ነው ሲሉ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ(ዶ/ር) ገለፁ
ተፈላጊነቱ እየጨመረ የመጣውን የቆጮ ምግብ ጥራትና ተደራሽነት ከፍ ለማድረግ የሚያስችሉ የምርምር ስራዎች እያከናወነ መሆኑን በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የብሔራዊ ግብርና ባዮ ቴክኖሎጂ ምርምር ማዕከል ገለጸ