ፀሐይ አውሮፕላን ዛሬ አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ስትደርስ ደማቅ አቀባበል ተደረገላት
ሀዋሳ፡ የካቲት 01/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ፀሐይ አውሮፕላን ከበርካታ ዓመታት በኋላ ዛሬ አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ስትደርስ በደመቀ ሁኔታ አቀባበል ተደርጎላታል።
እ.አ.አ በ1935 ዓ.ም በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ግዜ ተገጣጥማ በረራ ያደረገችው ፀሐይ አውሮፕላን ከበርካታ ዓመታት በኋላ ዛሬ አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ስትደርስ በደመቀ ሁኔታ አቀባበል እንደተደረገላት የኢትዮጵያ አየር መንገድ መረጃ ያመላክታል።
በጀርመናዊው ኢንጅነር ሄር ሉድዊግ ዌበር እና የኢትዮጵያ ባለሞያዎች ትብብር የተሰራችው “ፀሐይ” አውሮፕላን በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዲፕሎማሲ ጥረት ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ መብቃቷ ይታወቃል።

More Stories
የአየር ንብረት ለውጥ መቋቋም የሚችል ዘላቂ የግብርና ኢኮኖሚ መገንባት እንደሚገባ ተገለጸ
ከ230 ሺህ በላይ ዜጎች የፋይዳ ዲጅታል መታወቂያ መውሰዳቸውን የሀላባ ዞን ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት መምሪያ አስታወቀ
ብሔራዊ ምክክር ሀገራዊ አንድነትን ከማጠናከር ባሻገር ችግሮችን በውይይትና በሀሳብ የበላይነት ለመፍታት መሠረት እንደሚጥል ተገለጸ