የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የጠቅላይ፣ ከፍተኛና ወረዳ ፍርድ ቤቶች ዳኞችን ሹመት አፀደቀ
የክልሉ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ቆጭቶ ገብረ ማርያም በምልመላውና መረጣው ያለፉ ዳኞችን ለጉባኤው አቅርበዋል።
ነፃና ገለልተኛ ዳኝነትን ለማሳደግ የወጡ የምልመላ መስፈርቶችን ያሟሉትን የፅሁፍ ፈተናም በመፈተን፤ የዳኝነት ስነምግባርንም ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የተለያዩ ማጣሪያዎችን በዳኞች ጉባኤም በማካሄድ ለሹመት መቅረባቸውን አብራርተዋል።
የተሾሙ ዳኞችም ለክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ ለዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች፣ ለወረዳና ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤቶች መሆናቸውም ተገልጿል።
በቀረቡ ዕጩዎች ዙሪያ ሀሳብና አስተያየት ተሰጥቶ የ66 ዳኞች ሹመት በአባላቱ ሙሉ ድምፅ ፀድቋል።
በምክር ቤቱ የተሾሙ ዳኞችም ቃለመሃላ ፈፅመዋል።
ከትላንት ጀምሮ ሲካሄድ የነበረው የክልሉ ምክር ቤት ጉባዔም ተጠናቋል።
ዘጋቢ፡ ዮሐንስ መካሻ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
ፋይዳ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ የህዝብና የመንግስት አገልግሎቶችን የሚያፋጥን በመሆኑ ለሁሉም ለማድረስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ
ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የእርስ በርስ ግንኙነትና አንድነትን የሚያጠናክር ተግባር መሆኑ ተገለጸ
በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል አለባቸዉ – ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ