የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የጠቅላይ፣ ከፍተኛና ወረዳ ፍርድ ቤቶች ዳኞችን ሹመት አፀደቀ
የክልሉ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ቆጭቶ ገብረ ማርያም በምልመላውና መረጣው ያለፉ ዳኞችን ለጉባኤው አቅርበዋል።
ነፃና ገለልተኛ ዳኝነትን ለማሳደግ የወጡ የምልመላ መስፈርቶችን ያሟሉትን የፅሁፍ ፈተናም በመፈተን፤ የዳኝነት ስነምግባርንም ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የተለያዩ ማጣሪያዎችን በዳኞች ጉባኤም በማካሄድ ለሹመት መቅረባቸውን አብራርተዋል።
የተሾሙ ዳኞችም ለክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ ለዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች፣ ለወረዳና ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤቶች መሆናቸውም ተገልጿል።
በቀረቡ ዕጩዎች ዙሪያ ሀሳብና አስተያየት ተሰጥቶ የ66 ዳኞች ሹመት በአባላቱ ሙሉ ድምፅ ፀድቋል።
በምክር ቤቱ የተሾሙ ዳኞችም ቃለመሃላ ፈፅመዋል።
ከትላንት ጀምሮ ሲካሄድ የነበረው የክልሉ ምክር ቤት ጉባዔም ተጠናቋል።
ዘጋቢ፡ ዮሐንስ መካሻ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
በወሊድ ምክንያት የሚሞቱ እናቶችን ቁጥር ለመቀነስ የተጀመሩ ስራዎች አበረታች ውጤት እያስመዘገቡ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ
የፃማኮ ብሄረሰብ የዘመን መለወጫ የ”ባርባይሳ” በዓል የህብረ ብሄራዊ አንድነት መገለጫ፣ የሰላምና የመተሳሰብ ምልክትነቱን በማግዘፍ ለዓለም አደባባይ ማብቃት ይገባል ሲሉ የክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ገለጹ
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ