የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የጠቅላይ፣ ከፍተኛና ወረዳ ፍርድ ቤቶች ዳኞችን ሹመት አፀደቀ
የክልሉ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ቆጭቶ ገብረ ማርያም በምልመላውና መረጣው ያለፉ ዳኞችን ለጉባኤው አቅርበዋል።
ነፃና ገለልተኛ ዳኝነትን ለማሳደግ የወጡ የምልመላ መስፈርቶችን ያሟሉትን የፅሁፍ ፈተናም በመፈተን፤ የዳኝነት ስነምግባርንም ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የተለያዩ ማጣሪያዎችን በዳኞች ጉባኤም በማካሄድ ለሹመት መቅረባቸውን አብራርተዋል።
የተሾሙ ዳኞችም ለክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ ለዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች፣ ለወረዳና ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤቶች መሆናቸውም ተገልጿል።
በቀረቡ ዕጩዎች ዙሪያ ሀሳብና አስተያየት ተሰጥቶ የ66 ዳኞች ሹመት በአባላቱ ሙሉ ድምፅ ፀድቋል።
በምክር ቤቱ የተሾሙ ዳኞችም ቃለመሃላ ፈፅመዋል።
ከትላንት ጀምሮ ሲካሄድ የነበረው የክልሉ ምክር ቤት ጉባዔም ተጠናቋል።
ዘጋቢ፡ ዮሐንስ መካሻ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ከዳር ለማድረስ በሚደረገው ርብርብ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሙዱላ ከተማ አስተዳደር ገለፀ
በትምህርት ሴክተር የመረጃ አያያዝ ውጤታማነት ዙሪያ በኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ
ሁሉንም የመማሪያ መጻሕፍት ባለማግኘታቸው በትምህርታቸው ላይ ጫና እየፈጠረባቸው መሆኑን በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የቆንጋና ቆቄ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተናገሩ