ጥራት ያለው ፍትህ ዜጎች ማግኘት እንዲችሉ በዘርፉ ያሉ ተቋማት በልዩ ትኩረት መሥራት እንዳለባቸው ተገለፀ

የአሪ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የ2016 የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም የውይይት መድረክ ከወረዳና ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤቶች እንዲሁም ከባለድርሻ አካላት ጋር እየተካሄደ ይገኛል።

የውይይት መድረኩን በንግግር የከፈቱት የአሪ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ አንተነህ በላይ፤ ህዝቡ በተቋሙ በሚረካ መልኩ የዳኝነት ሥራው እንዲከናወን እየተሠራ መሆኑን ገልፀው በግማሽ ዓመት የተከናወኑ ተግባራትን ተሳታፊዎች በጥልቀት በመገምገም ችግሮች እንዲለዩና ጥንካሬዎች ጎልብተው እንዲቀጥሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በመድረኩ የተከናወኑ ተግባራት ሪፖርት እየቀረበ ሲሆን ተሳታፊዎች ገንቢ አስተያየቶችን ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን