የአሪ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የ2016 የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም የውይይት መድረክ ከወረዳና ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤቶች እንዲሁም ከባለድርሻ አካላት ጋር እየተካሄደ ይገኛል።
የውይይት መድረኩን በንግግር የከፈቱት የአሪ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ አንተነህ በላይ፤ ህዝቡ በተቋሙ በሚረካ መልኩ የዳኝነት ሥራው እንዲከናወን እየተሠራ መሆኑን ገልፀው በግማሽ ዓመት የተከናወኑ ተግባራትን ተሳታፊዎች በጥልቀት በመገምገም ችግሮች እንዲለዩና ጥንካሬዎች ጎልብተው እንዲቀጥሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በመድረኩ የተከናወኑ ተግባራት ሪፖርት እየቀረበ ሲሆን ተሳታፊዎች ገንቢ አስተያየቶችን ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳ ከ22 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ለሚገነባው የእንስሳት ግብይት ማዕከል ግንባታ የሳይት ርክክብ ተደረገ
የሀገራችንን ብልፅግና እውን ለማድረግ በበቂ ዕውቀትና ክህሎት የታነፁ ምሁራንን በማፍራት የተሻለ ትውልድ መቅረጽ ቁልፍ ተግባር ነው ሲሉ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ(ዶ/ር) ገለፁ
ተፈላጊነቱ እየጨመረ የመጣውን የቆጮ ምግብ ጥራትና ተደራሽነት ከፍ ለማድረግ የሚያስችሉ የምርምር ስራዎች እያከናወነ መሆኑን በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የብሔራዊ ግብርና ባዮ ቴክኖሎጂ ምርምር ማዕከል ገለጸ