የአሪ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የ2016 የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም የውይይት መድረክ ከወረዳና ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤቶች እንዲሁም ከባለድርሻ አካላት ጋር እየተካሄደ ይገኛል።
የውይይት መድረኩን በንግግር የከፈቱት የአሪ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ አንተነህ በላይ፤ ህዝቡ በተቋሙ በሚረካ መልኩ የዳኝነት ሥራው እንዲከናወን እየተሠራ መሆኑን ገልፀው በግማሽ ዓመት የተከናወኑ ተግባራትን ተሳታፊዎች በጥልቀት በመገምገም ችግሮች እንዲለዩና ጥንካሬዎች ጎልብተው እንዲቀጥሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በመድረኩ የተከናወኑ ተግባራት ሪፖርት እየቀረበ ሲሆን ተሳታፊዎች ገንቢ አስተያየቶችን ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ 25 ሺህ 338 ሊትር ቤንዝልና 62 ሺ 686 ሊትር ናፍጣ በቁጥጥር ስር መዋሉን የክልሉ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ አስታወቀ
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ