የአሪ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የ2016 የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም የውይይት መድረክ ከወረዳና ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤቶች እንዲሁም ከባለድርሻ አካላት ጋር እየተካሄደ ይገኛል።
የውይይት መድረኩን በንግግር የከፈቱት የአሪ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ አንተነህ በላይ፤ ህዝቡ በተቋሙ በሚረካ መልኩ የዳኝነት ሥራው እንዲከናወን እየተሠራ መሆኑን ገልፀው በግማሽ ዓመት የተከናወኑ ተግባራትን ተሳታፊዎች በጥልቀት በመገምገም ችግሮች እንዲለዩና ጥንካሬዎች ጎልብተው እንዲቀጥሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በመድረኩ የተከናወኑ ተግባራት ሪፖርት እየቀረበ ሲሆን ተሳታፊዎች ገንቢ አስተያየቶችን ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በወሊድ ምክንያት የሚሞቱ እናቶችን ቁጥር ለመቀነስ የተጀመሩ ስራዎች አበረታች ውጤት እያስመዘገቡ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ
የፃማኮ ብሄረሰብ የዘመን መለወጫ የ”ባርባይሳ” በዓል የህብረ ብሄራዊ አንድነት መገለጫ፣ የሰላምና የመተሳሰብ ምልክትነቱን በማግዘፍ ለዓለም አደባባይ ማብቃት ይገባል ሲሉ የክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ገለጹ
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ