ምክር ቤቱ የፍትሕ ሚኒስቴርን የ6 ወር የስራ አፈጻጸም ሪፖርት እያዳመጠ ነው
ሀዋሳ፡ ጥር 23/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የሚኒስቴሩ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) ባለፉት 6 ወራት ለ 6ሺ 13 ዜጎች ነጻ የሕግ አገልግሎት የተሰጠ መሆኑን በሪፖርታቸው አመላክተው የህም የዕቅዱ መቶ ፐርሰንት መፈጸሙን ገልጸዋል፡፡
ሚኒስትሩ ለ58 ሺህ 4 መቶ 78 በማረሚያ ቤትና በፖሊስ ማረፊያ ቤት በሕግ ቁጥጥር ስር የዋሉ ታራሚዎችን በመጎብኘት በተገኙ ግኝቶች ላይ የእርምት እርምጃ መወሰዱን ገልጸዋል፡፡
እንደ ሚኒስቴሩ ገለጻ በሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማሳደግ በተሰራው ስራ ከደቡብ አፍሪካ መንግስት ጋር በወንጀል የሚፈለጉ ሰዎችን አሳልፎ የመስጠት ስምምነት ተፈርሟል፡፡
በተጨማሪም ከደቡብ ሱዳን፣ ከቦትስዋና እና ከቻይና መንግስት ጋር በአሳልፎ መስጠትና በወንጀል ጉዳዮች የጋራ የህግ ትብብር የሁለትዮሽ ስምምነቶችን ለማድረግ ረቂቅ ስምምነቶች ተዘጋጅተው ለሚመለከታቸውና ለባለድርሻ አካላት ተደራሽ መደረጋቸውን ሚኒስትሩ በሪፖርታቸው ማመላከታቸውን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መረጃ ያሳያል፡፡

More Stories
በዶሮ እርባታ ዘርፍ በመሰማራት የተሻለ ውጤት እያስመዘገቡ መሆናቸውን የየም ዞን ሣጃ ከተማ በዘርፉ የተሰማሩ ሰዎች ተናገሩ
የከተማውን መሰረተ ልማት ከማሟላት ባሻገር ለነዋሪዎች ምቹ እና ማራኪ በማድረግ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ
የዱራሜ ከተማ የኮሪደር ልማት ሥራ በአዲስ መልክ በዘመናዊ ዲዛይን እየተሰራ መሆኑን የዱራሜ ከተማ አስተዳደር ገለፀ