ምክር ቤቱ የፍትሕ ሚኒስቴርን የ6 ወር የስራ አፈጻጸም ሪፖርት እያዳመጠ ነው
ሀዋሳ፡ ጥር 23/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የሚኒስቴሩ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) ባለፉት 6 ወራት ለ 6ሺ 13 ዜጎች ነጻ የሕግ አገልግሎት የተሰጠ መሆኑን በሪፖርታቸው አመላክተው የህም የዕቅዱ መቶ ፐርሰንት መፈጸሙን ገልጸዋል፡፡
ሚኒስትሩ ለ58 ሺህ 4 መቶ 78 በማረሚያ ቤትና በፖሊስ ማረፊያ ቤት በሕግ ቁጥጥር ስር የዋሉ ታራሚዎችን በመጎብኘት በተገኙ ግኝቶች ላይ የእርምት እርምጃ መወሰዱን ገልጸዋል፡፡
እንደ ሚኒስቴሩ ገለጻ በሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማሳደግ በተሰራው ስራ ከደቡብ አፍሪካ መንግስት ጋር በወንጀል የሚፈለጉ ሰዎችን አሳልፎ የመስጠት ስምምነት ተፈርሟል፡፡
በተጨማሪም ከደቡብ ሱዳን፣ ከቦትስዋና እና ከቻይና መንግስት ጋር በአሳልፎ መስጠትና በወንጀል ጉዳዮች የጋራ የህግ ትብብር የሁለትዮሽ ስምምነቶችን ለማድረግ ረቂቅ ስምምነቶች ተዘጋጅተው ለሚመለከታቸውና ለባለድርሻ አካላት ተደራሽ መደረጋቸውን ሚኒስትሩ በሪፖርታቸው ማመላከታቸውን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መረጃ ያሳያል፡፡
More Stories
በወላይታ ዞን ባለፉት 10 ወራት ውስጥ ህገ-ወጥ ንግድና ለመከላከል በተደረገው ክትትል 2 ሺህ 135 ነጋዴዎች ላይ የእርምት እርምጃ መውሰድ መቻሉን የዞኑ ንግድና ገበያ ልማት መመሪያ አስታወቀ
በ2017/18 የመኸር አዝመራ ከ4 መቶ ሺ ሄክታር በላይ ማሳን በተለያዩ የሰብል ዓይነቶች መሸፈኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት የ10 ወራት አፈጻጸም እና የቀጣይ የክረምት ወራት ቅድመ ዝግጅት ግምገማ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ እያካሄደ ይገኛል