ምክር ቤቱ የፍትሕ ሚኒስቴርን የ6 ወር የስራ አፈጻጸም ሪፖርት እያዳመጠ ነው
ሀዋሳ፡ ጥር 23/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የሚኒስቴሩ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) ባለፉት 6 ወራት ለ 6ሺ 13 ዜጎች ነጻ የሕግ አገልግሎት የተሰጠ መሆኑን በሪፖርታቸው አመላክተው የህም የዕቅዱ መቶ ፐርሰንት መፈጸሙን ገልጸዋል፡፡
ሚኒስትሩ ለ58 ሺህ 4 መቶ 78 በማረሚያ ቤትና በፖሊስ ማረፊያ ቤት በሕግ ቁጥጥር ስር የዋሉ ታራሚዎችን በመጎብኘት በተገኙ ግኝቶች ላይ የእርምት እርምጃ መወሰዱን ገልጸዋል፡፡
እንደ ሚኒስቴሩ ገለጻ በሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማሳደግ በተሰራው ስራ ከደቡብ አፍሪካ መንግስት ጋር በወንጀል የሚፈለጉ ሰዎችን አሳልፎ የመስጠት ስምምነት ተፈርሟል፡፡
በተጨማሪም ከደቡብ ሱዳን፣ ከቦትስዋና እና ከቻይና መንግስት ጋር በአሳልፎ መስጠትና በወንጀል ጉዳዮች የጋራ የህግ ትብብር የሁለትዮሽ ስምምነቶችን ለማድረግ ረቂቅ ስምምነቶች ተዘጋጅተው ለሚመለከታቸውና ለባለድርሻ አካላት ተደራሽ መደረጋቸውን ሚኒስትሩ በሪፖርታቸው ማመላከታቸውን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መረጃ ያሳያል፡፡

More Stories
የማህበረሰቡን የፍትህ ጥማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ተገቢ ምላሽ እንዲያገኙ ተቀናጅቶ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ዘመናዊ የመሬት ሕግ ሥርዓት መዘርጋትና ተቋማዊ አቅምን መገንባት ለሀገር ዕድገት ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ
አብሮነት፣ ፍቅርና አንድነት የሚነግስበት ታላቁ የረመዳን ወር የኢፍጣር ሥነ-ሥርዓት በጀንካ ከተማ ተካሄደ