የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 13ኛ መደበኛ ስብሰባውን ዛሬ ያካሂዳል
ሀዋሳ፡ ጥር 23/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) 6ኛው ዙር የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 13ኛ መደበኛ ስብሰባውን ዛሬ ያካሄዳል፡፡
ምክር ቤቱ በዛሬው መደበኛ ስብሰባው ቀዳሚ አጀንዳ የሆነውን የ12ኛ መደበኛ ስብሰባን ቃለ ጉባዔ የሚያፀድቅ ይሆናል፡፡
በመቀጥልም የፍትህ ሚኒስቴር የ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ግማሽ ዓመት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በማዳመጥ በምክር ቤቱ አባላት ውይይት ይደረግበታል፡፡
ምንጭ ፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት

More Stories
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ
በከተማው በተያዘው በጀት ዓመት በ5 ወራት ውስጥ 1 ቢሊየን 5 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ
የሰራተኞች የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበር ብዙዎችን የቤት ባለቤት ማድረጉ ተገለጸ