በስፖርቱ ዘርፍ የጀመራቸውን ሥራዎች በማጠናከር ለማህበረሰቡ ተጠቃሚነት አንደሚሠራ ዩኒቨርሲቲው ገለፀ
ሀዋሳ፡ ጥቅምት 14/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በስፖርቱ ዘርፍ የጀመራቸውን ሥራዎች በማጠናከር ለማህበረሰቡ ተጠቃሚነት አንደሚሠራ የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ገልጿል፡፡
ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ሥራው በተጨማሪ የአከባቢው ማህበረሰብ በዘመናዊ ታግዞ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እንዲያደርግ የድርሻቸውን እየተወጣ ይገኛል፡፡
በዩኒቨርሲቲው ግቢ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በማድረግ ተላላፊ ካልሆኑ በሽታዎች ራሳቸውን መጠበቅ መቻላቸውን የአካል ብቃት ሠሪዎች ገልፀዋል፡፡
በስፖርቱ ዘርፍ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዩኒቨርሲቲው የሚያደርገውን ጥረት ውጤታማ ለማድረግ ድጋፍ እንደሚያደርጉ በጂንካ ዩኒቨርሲቲ የስፖርት ክፍል መምህራን ተናግረዋል፡፡
በጂንካ ዩኒቨርሲቲ በተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ የስፖርት ሳይንስ ትምህርት ክፍል ኃላፊ አቶ አሚን ዓሊ እንደገለፀት፤ የዩኒቨርሲቲውን ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከ 17 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ ዘመናዊ የጂሚናስትክ መሣሪያዎች ተገዝተው አገልግሎት እየሰጡ እንዳለም አስረድተዋል፡፡
ኃላፊው አክለውም ህብረተሰቡ የአካል ብቃት እንቅስቃሴን በማዳበር ጤናውን እንዲጠብቅ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ተመስገን አሰፋ – ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በጎፋ ዞን በመሬት መንሸራተት ጉዳት የደረሰባቸውን ዜጎች በስፍራው ተገኝተው አፅናኑ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ከንቾ ሻቻ ጎዚዲ ቀበሌ በተከሰተው የመሬት መንሽራት አደጋ ምክንያት ህይወታቸውን ያጡ ወገኖቻችንን በማሰብ ከሐምሌ 20/2016 ዓ.ም ጀምሮ ለ3 ተከታታይ ቀናት ብሔራዊ የሀዘን ቀን ታውጇል
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በጎፋ ዞን በመሬት መንሸራተት ጉዳት የደረሰባቸውን ዜጎች በስፍራው ተገኝተው አፅናኑ