በስፖርቱ ዘርፍ የጀመራቸውን ሥራዎች በማጠናከር ለማህበረሰቡ ተጠቃሚነት አንደሚሠራ ዩኒቨርሲቲው ገለፀ
ሀዋሳ፡ ጥቅምት 14/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በስፖርቱ ዘርፍ የጀመራቸውን ሥራዎች በማጠናከር ለማህበረሰቡ ተጠቃሚነት አንደሚሠራ የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ገልጿል፡፡
ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ሥራው በተጨማሪ የአከባቢው ማህበረሰብ በዘመናዊ ታግዞ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እንዲያደርግ የድርሻቸውን እየተወጣ ይገኛል፡፡
በዩኒቨርሲቲው ግቢ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በማድረግ ተላላፊ ካልሆኑ በሽታዎች ራሳቸውን መጠበቅ መቻላቸውን የአካል ብቃት ሠሪዎች ገልፀዋል፡፡
በስፖርቱ ዘርፍ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዩኒቨርሲቲው የሚያደርገውን ጥረት ውጤታማ ለማድረግ ድጋፍ እንደሚያደርጉ በጂንካ ዩኒቨርሲቲ የስፖርት ክፍል መምህራን ተናግረዋል፡፡
በጂንካ ዩኒቨርሲቲ በተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ የስፖርት ሳይንስ ትምህርት ክፍል ኃላፊ አቶ አሚን ዓሊ እንደገለፀት፤ የዩኒቨርሲቲውን ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከ 17 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ ዘመናዊ የጂሚናስትክ መሣሪያዎች ተገዝተው አገልግሎት እየሰጡ እንዳለም አስረድተዋል፡፡
ኃላፊው አክለውም ህብረተሰቡ የአካል ብቃት እንቅስቃሴን በማዳበር ጤናውን እንዲጠብቅ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ተመስገን አሰፋ – ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
አቶ ጌታቸው ኬኒ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብሄረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ሆነው ተሾሙ
ባለፉት ጊዜያት በህዝብና በመንግስት መካከል ያለውን ግንኙነት ያጠናከሩ ተግባራት መከናወናቸውን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ገለጸ
የኮሪደር ልማት ሥራ ከተማን ዉብ፣ ሳቢና ለነዋሪዎች ምቹ ከማድረግ ባለፈ ለበርካታ ወጣቶች ሥራ ዕድል መፍጠር መቻሉን የዳዉሮ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ አስታወቀ