በስፖርቱ ዘርፍ የጀመራቸውን ሥራዎች በማጠናከር ለማህበረሰቡ ተጠቃሚነት አንደሚሠራ ዩኒቨርሲቲው ገለፀ
ሀዋሳ፡ ጥቅምት 14/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በስፖርቱ ዘርፍ የጀመራቸውን ሥራዎች በማጠናከር ለማህበረሰቡ ተጠቃሚነት አንደሚሠራ የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ገልጿል፡፡
ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ሥራው በተጨማሪ የአከባቢው ማህበረሰብ በዘመናዊ ታግዞ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እንዲያደርግ የድርሻቸውን እየተወጣ ይገኛል፡፡
በዩኒቨርሲቲው ግቢ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በማድረግ ተላላፊ ካልሆኑ በሽታዎች ራሳቸውን መጠበቅ መቻላቸውን የአካል ብቃት ሠሪዎች ገልፀዋል፡፡
በስፖርቱ ዘርፍ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዩኒቨርሲቲው የሚያደርገውን ጥረት ውጤታማ ለማድረግ ድጋፍ እንደሚያደርጉ በጂንካ ዩኒቨርሲቲ የስፖርት ክፍል መምህራን ተናግረዋል፡፡
በጂንካ ዩኒቨርሲቲ በተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ የስፖርት ሳይንስ ትምህርት ክፍል ኃላፊ አቶ አሚን ዓሊ እንደገለፀት፤ የዩኒቨርሲቲውን ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከ 17 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ ዘመናዊ የጂሚናስትክ መሣሪያዎች ተገዝተው አገልግሎት እየሰጡ እንዳለም አስረድተዋል፡፡
ኃላፊው አክለውም ህብረተሰቡ የአካል ብቃት እንቅስቃሴን በማዳበር ጤናውን እንዲጠብቅ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ተመስገን አሰፋ – ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
በዞኑ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአርሶ አደሩ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ በግብርናው ዘርፍ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በትኩረት እንደሚሰራ የጋሞ ዞን አሰተዳደር አሰታወቀ
በሀሳብ ልዕልና የሚያምን የፖለቲካ ሥነ-ምህዳርን በማስፋት ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በመመካከርና በመደጋገፍ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
የኢፌዲሪ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ከ82 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ መቆርቆር ቀበሌ ያስገነባው የንጹህ መጠ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ