በስፖርቱ ዘርፍ የጀመራቸውን ሥራዎች በማጠናከር ለማህበረሰቡ ተጠቃሚነት አንደሚሠራ ዩኒቨርሲቲው ገለፀ
ሀዋሳ፡ ጥቅምት 14/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በስፖርቱ ዘርፍ የጀመራቸውን ሥራዎች በማጠናከር ለማህበረሰቡ ተጠቃሚነት አንደሚሠራ የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ገልጿል፡፡
ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ሥራው በተጨማሪ የአከባቢው ማህበረሰብ በዘመናዊ ታግዞ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እንዲያደርግ የድርሻቸውን እየተወጣ ይገኛል፡፡
በዩኒቨርሲቲው ግቢ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በማድረግ ተላላፊ ካልሆኑ በሽታዎች ራሳቸውን መጠበቅ መቻላቸውን የአካል ብቃት ሠሪዎች ገልፀዋል፡፡
በስፖርቱ ዘርፍ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዩኒቨርሲቲው የሚያደርገውን ጥረት ውጤታማ ለማድረግ ድጋፍ እንደሚያደርጉ በጂንካ ዩኒቨርሲቲ የስፖርት ክፍል መምህራን ተናግረዋል፡፡
በጂንካ ዩኒቨርሲቲ በተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ የስፖርት ሳይንስ ትምህርት ክፍል ኃላፊ አቶ አሚን ዓሊ እንደገለፀት፤ የዩኒቨርሲቲውን ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከ 17 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ ዘመናዊ የጂሚናስትክ መሣሪያዎች ተገዝተው አገልግሎት እየሰጡ እንዳለም አስረድተዋል፡፡
ኃላፊው አክለውም ህብረተሰቡ የአካል ብቃት እንቅስቃሴን በማዳበር ጤናውን እንዲጠብቅ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ተመስገን አሰፋ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ