የመደመር ጉዞ በሚል ርዕስ የውይይት መድረክ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ጥቅምት 14/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከኢትዮጽያ ዜና አገልግሎት ጋር በመተባበር የመደመር ጉዞ በሚል ርዕስ የተዘጋጀው የውይይት መድረክ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ በመካሄድ ላይ ነዉ ።
በውይይት መድረኩ ላይ የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው፣ የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች እንዲሁም የሀይማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎች በውይይቱ መድረኩ ተገኝተዋል።
ሰለመደመርና አብይ ትርክት፣ የመደመር ዕሴት የፈጠረው ጸጋ ለማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች እና በሌሎችም የተለያዩ ጥናታዊ ጹሁፎች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው የውይይት መድረኩ በመምራት ላይ ሲሆኑ የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽ አማካሪ ዶክተር ቢቂላ ሁሪሳ በመደመርና አብይ ትርክት ዙሪያ የውይይት መነሻ ጽሁፍ አቅርበዋል፡፡
የመደመር ዕሳቤን ላይ ግንዛቤ በመፍጠር ሀገራዊ መግባባትን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሻገር እንዲረዳ ታሳቢ ያደረገ መድረክ መሆኑ ተገልጿል ።
ዘጋቢ:- ፋሲል ሀይሉ
More Stories
የሸኮ ከተማ አስተዳደር በመደራጀቱ የተለያዩ መንግስታዊ አገለግሎቶችን በአቅራቢያ ማገኘታቸው እንዳስደሰታቸው የከተማው ነዋሪዎች ገለፁ
በተለያየ ዘርፍ በማህበር በመደራጀት ተጠቃሚ መሆናቸውን በሐመር ወረዳ በማህበር የተደራጁ ወጣቶች ተናገሩ
የጎፋ ዞን ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ በዞኑ ለሚገኙ 50 አካል ጉዳተኞች 3 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር የሚገመት የዊልቸር ድጋፍ አደረገ