የመደመር ጉዞ በሚል ርዕስ የውይይት መድረክ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ጥቅምት 14/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከኢትዮጽያ ዜና አገልግሎት ጋር በመተባበር የመደመር ጉዞ በሚል ርዕስ የተዘጋጀው የውይይት መድረክ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ በመካሄድ ላይ ነዉ ።
በውይይት መድረኩ ላይ የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው፣ የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች እንዲሁም የሀይማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎች በውይይቱ መድረኩ ተገኝተዋል።
ሰለመደመርና አብይ ትርክት፣ የመደመር ዕሴት የፈጠረው ጸጋ ለማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች እና በሌሎችም የተለያዩ ጥናታዊ ጹሁፎች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው የውይይት መድረኩ በመምራት ላይ ሲሆኑ የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽ አማካሪ ዶክተር ቢቂላ ሁሪሳ በመደመርና አብይ ትርክት ዙሪያ የውይይት መነሻ ጽሁፍ አቅርበዋል፡፡
የመደመር ዕሳቤን ላይ ግንዛቤ በመፍጠር ሀገራዊ መግባባትን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሻገር እንዲረዳ ታሳቢ ያደረገ መድረክ መሆኑ ተገልጿል ።
ዘጋቢ:- ፋሲል ሀይሉ
More Stories
ስፖርት በአንድ አካባቢ የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ከማቀራረቡም በተጨማሪም ለአንድ አካባቢ ሰላም መስፈን ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት የጉራጌ ዞን አስተዳደር ገለጸ
አምረፍ ሄልዝ አፍሪካ ግብረ ሰናይ ድርጅት ለበርካታ ዓመታት የጤናውን ዘርፍ በመደገፍ የማይተካ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ
ከእርሻ መሬት መጠቀሚያ ግብር 20 ሚሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀዲያ ዞን የጎምቦራ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ ቤት አስታወቀ