የመደመር ጉዞ በሚል ርዕስ የውይይት መድረክ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ጥቅምት 14/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከኢትዮጽያ ዜና አገልግሎት ጋር በመተባበር የመደመር ጉዞ በሚል ርዕስ የተዘጋጀው የውይይት መድረክ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ በመካሄድ ላይ ነዉ ።
በውይይት መድረኩ ላይ የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው፣ የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች እንዲሁም የሀይማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎች በውይይቱ መድረኩ ተገኝተዋል።
ሰለመደመርና አብይ ትርክት፣ የመደመር ዕሴት የፈጠረው ጸጋ ለማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች እና በሌሎችም የተለያዩ ጥናታዊ ጹሁፎች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው የውይይት መድረኩ በመምራት ላይ ሲሆኑ የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽ አማካሪ ዶክተር ቢቂላ ሁሪሳ በመደመርና አብይ ትርክት ዙሪያ የውይይት መነሻ ጽሁፍ አቅርበዋል፡፡
የመደመር ዕሳቤን ላይ ግንዛቤ በመፍጠር ሀገራዊ መግባባትን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሻገር እንዲረዳ ታሳቢ ያደረገ መድረክ መሆኑ ተገልጿል ።
ዘጋቢ:- ፋሲል ሀይሉ

More Stories
የፍትህ ስርዓቱን ተደራሽና ቀልጣፋ ለማድረግ እየተሰራ ነዉ – የካፋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማ እንዲሆን ሴቶች በግንባር ቀደምነት በመሳተፍ የበኩላቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተገለጸ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮ የ2018 በጀት አመት የመጀመሪያ ግማሽ አመት አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በዱራሜ ከተማ እየተካሄደ ነው