ሀዋሳ፡ ጥቅምት 13/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በኮሬ ዞን የማልማት ዕቅድ ዙሪያ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር የውይይት መድረክ በኬሌ ከተማ በተካሄደበት ወቅት አከባቢን ለማልማት እጅ ለእጅ መያያዝ እንደሚጠበቅ ተመላክቷል።
የውይይቱን ሰነድ ያቀረቡት የሀብት አሰባሰብ ኮሚቴ አቶ ዮሐንስ ኃይሉ እንደገለጹት፤ ዞኑን ለማልማት በአጭርና በረጅም ጊዜ ዕቅድ የተያዘ ሲሆን በ2016 የበጀት ዓመት ለመሥራት ከታቀዱት ባለሰንሰለት እስካባተርና ዶዞር ግዥ እና ከአልፋጮ ነጭ ሣር ወደ አርባ ምንጭ የሚወስደው መንገድ ሥራ ተጠቃሾች ናቸው።
በቀጣይም 5 ዓመት ዕቅድ ውስጥ 2 የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች በ2ቱ ወረዳ መገንባትና ነባሩን ሆስፒታል ወደ አጠቃላይ ለማሳደግ ግብ መጣሉን ከሪፖርቱ አይተናል።
ዞኑን ማልማት የሚችለው ማህበረሰብ እንደሆነ የገለጹት የኮሬ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ታረቀኝ በቀለ ከህብረተሰቡ ጋር በመወያየትና ምክረ-ሃሳብ ተቀብሎ መተገበር ለዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለውም ተናግረዋል::

More Stories
የፍትህ ስርዓቱን ተደራሽና ቀልጣፋ ለማድረግ እየተሰራ ነዉ – የካፋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማ እንዲሆን ሴቶች በግንባር ቀደምነት በመሳተፍ የበኩላቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተገለጸ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮ የ2018 በጀት አመት የመጀመሪያ ግማሽ አመት አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በዱራሜ ከተማ እየተካሄደ ነው