ሀዋሳ፡ ጥቅምት 13/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በኮሬ ዞን የማልማት ዕቅድ ዙሪያ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር የውይይት መድረክ በኬሌ ከተማ በተካሄደበት ወቅት አከባቢን ለማልማት እጅ ለእጅ መያያዝ እንደሚጠበቅ ተመላክቷል።
የውይይቱን ሰነድ ያቀረቡት የሀብት አሰባሰብ ኮሚቴ አቶ ዮሐንስ ኃይሉ እንደገለጹት፤ ዞኑን ለማልማት በአጭርና በረጅም ጊዜ ዕቅድ የተያዘ ሲሆን በ2016 የበጀት ዓመት ለመሥራት ከታቀዱት ባለሰንሰለት እስካባተርና ዶዞር ግዥ እና ከአልፋጮ ነጭ ሣር ወደ አርባ ምንጭ የሚወስደው መንገድ ሥራ ተጠቃሾች ናቸው።
በቀጣይም 5 ዓመት ዕቅድ ውስጥ 2 የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች በ2ቱ ወረዳ መገንባትና ነባሩን ሆስፒታል ወደ አጠቃላይ ለማሳደግ ግብ መጣሉን ከሪፖርቱ አይተናል።
ዞኑን ማልማት የሚችለው ማህበረሰብ እንደሆነ የገለጹት የኮሬ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ታረቀኝ በቀለ ከህብረተሰቡ ጋር በመወያየትና ምክረ-ሃሳብ ተቀብሎ መተገበር ለዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለውም ተናግረዋል::
More Stories
በዞኑ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአርሶ አደሩ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ በግብርናው ዘርፍ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በትኩረት እንደሚሰራ የጋሞ ዞን አሰተዳደር አሰታወቀ
በሀሳብ ልዕልና የሚያምን የፖለቲካ ሥነ-ምህዳርን በማስፋት ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በመመካከርና በመደጋገፍ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
የኢፌዲሪ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ከ82 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ መቆርቆር ቀበሌ ያስገነባው የንጹህ መጠ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ