ኢትዮጵያ ዛሬ ምሽት ተጨማሪ ሜዳሊያ ትጠብቃልች !!!
19ኛዉ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዎና መካሄዱን ቀጥሏል ።
በሃንጋሪ ቡዳፔስት ከተማ በመናወን ላይ የሚገኘው ሻምፒዮናው ዛሬ በአረተኛ ቀን ዉሎዉ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚሳተፉባቸው ሁለት የፍፃሜ ዉድድሮች ይካሄዳሉ ።
የሴቶች 1500 ሜትር እና የወንዶች 3000 ሜትር መሰናክል ፍፃሜ ከወዲሁ ወድድሮች የበርካቶችን ትኩረት ስበዋል ።
ምሽት 4:30 ሲል በሚጀመረው በሴቶች 1500ሜትር የፍፃሜ ዉድድር ላይ ድርቤ ወልተጂ እና ብርቄ ሃየሎም ኢትዮጵያን በመወከል ይወዳደራሉ ።
እንደ አዉሮፓዊያን አቆጣጠር በ 1997 አቴንስ በተደረገዉ ወድድር በርቀቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳፈችዉ ኢትዮጵያ ከሁለት ዓመት በኋላ በሲቪያ በተካሄደው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዎና የመጀመሪያውን ሜዳሊያ (ነሃስ ) በአትሌት ቁጥሬ ዱሌቻ አማካኝነት አገኘች ።
በ2015 እኤአ በጂንግ ላይ በገንዘቤ ዲባባ የመጀመሪያው የወርቅ ሜዳሊያ ለኢትዮጵያ በ 1500 ተገኝቷል ። አስካሁን አራት ሜዳሊያዎች በርቀቱ ኢትዮጲያ አግኝታለች ። ገንዘቤ ዲባባ (2015) ወርቅ ፣ ጉዳፍ ፀጋዬ (2022 ኦሪገን) ብር እና (2019ዶሃ ) ነሃስ እንዲሁም ቁጥሬ ዱሌቻ (1999 ሲቪያ ) የነሃስ ሜዳሊያን ለሃገራቸዉ ማምጣት ችለዋል ።
ዛሬ ምሽት በሚደረገዉ የፍፃሜ ዉድድር ከኢትዮጵያውያን አትሌቶች በተጨማሪ የርቀቱ የክብረወሰኑ ባለቤት የሆነችዉ እንዲሁም የ2017 እ 2022 የሻምፒዮናው አሸናፊ ኬኒያዊቷ አትሌት ፌይዝ ኪፕዬጎን እና የ2019 የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዎና የ1500ሜትር አሸናፊዋ ሲፋን ሃሰን በፍፃሜው ዉድድር ተሳታፊዎች ናቸዉ ።
ምሽት 4:42 ሲል በሚካሄደዉ በወንዶች 3000 ሜትር መሰናክል የፍፃሜ ዉድድር አትሌት ለሜቻ ግርማ እና አትሌት ጌትነት ዋለ ኢትዮጲያን ወክለዉ ይሮጣሉ ።
በጥሩ አቋም ላይ የሚገኙት አትሌቶቹ ለኢትዮጵያ በአትሌቲክስ ዉድድር ተሳትፎ ታሪክ በርቀቱ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ ለማምጣት እያለሙ ወደ ዉድድሩ ይገባሉ ።
በሶስት ትልልቅ ዉድድሮች ማለትም እኤአ 2019 በዶሀ ዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዎና ፣ በ 2020 የቶኪዮ ኦሎምፒክ እና በኦሪገን የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ለሃገሩ የብር ሜዳሊያ ማምጣት የቻለው እና የወቅቱ የርቀቱ የክብረወሰን ባለቤት ለሜቻ ግርማ ከሞሮኮዋዊው ሶፊያን ኤልባካሊ ጋር የሚያደርገው ትንቅንቅ ከወዲሁ አጓጊ ሆኗል ።
በዶሃ ፣ ቶኪዮ ኦሊምፒክ እና በኦሪገን ዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዎና አራተኛ ሆኖ በማጠናቀቅ ለሃገሩ ዲፕሎማዎችን ያስገኘዉና 8:05.15 የዓመቱ ምርጥ ሰዓት ያለዉ ጌትነት ዋለ የተሻለ ደረጃ ይዞ ሊያጠናቅቅ እንደሚችል ተገምቷል ።
የኬኒያዊያን የባህል እስፖርት ነዉ ተብሎ የሚነገርለት የ3000 ሜትር መሰናክል በቅርብ ዓመታት ዉስጥ ግን ከእጃቸዉ እየወጣ ይገኛል ። ከ18 የዓለም አትሌቲክ ሻምፒዎና በርቀቱ 13 ያሸነፉት ኬኒያዊያን ናቸው ። ዘንድሮስ ምን ያስመዘግቡ ይሆን ? ሲሞን ኪፕሮፕ ኮእች ፣ ቤንጃሚን ኪጋን እና አብርሃም ኪቢዎት የኬኒያን ክብር ለማስመለስ እያሰቡ ይወዳደራሉ ።
አዘጋጅ ፡ ሙሉቀን ባሳ
More Stories
2ኛው የየም ዞን ስፖርት ሻምፕዮና በሣጃ ከተማ እየተካሄደ ነው
የ2017 የጋሞ ዞን ልዩ ልዩ ስፖርቶች ሻምፒዮና ውድድር በወንዶች እግር ኳስ ውድድር በዳራማሎ ወረዳ አሸናፊነት ተጠናቀቀ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የጅቡቲ አቻውን 6ለ1 አሸነፈ