የጎፋ ዞን ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኢንስፔክተር ኃይሉ ወዳጆ ሀገራችን ኢትዮጵያ ችግሮችን በጽናት በመጋፈጥ በርካታ ድሎችን ማስመዝገቧን ተናግረው፤ ሕዝቡ የተጀመሩ ድሎችን ለማስቀጠል በጽናት ከጸጥታ አካላት ጋር መስራት እንዳለበት አሳስበዋል።
የሳውላ ከተማ ሰላምና ጸጥታ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ድንበሩ ደርቤ፤ የሀገርን ሠላም ማስጠበቅና ማፅናት የጋራ ትብብር ሰለሚጠይቅ የሚያጋጥሙ ፈተናዎችን በመቋቋም ሀገር የሚያሻግር ትውልድ ለመፍጠር በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገለጸዋል
ከሠላም ግንባታ ጎን በመሆን የተሰሩና እየተሰሩ ያሉ የልማት ሥራዎች በዘላቂነት እንዲቀጥሉ ሁሉም በጋራ ሊሰራ እንደሚገባም አሳስበዋል።
አስተያየታቸውን ያጋሩን የከተማዋ ነዋሪዎች፤ አባቶቻችን ትላንት የአድዋን ድል እንዳስመዘገቡት ሁሉ ዛሬ በአንድነትና በጽናት ተጋምደን ጠንካራ ሀገር በመገንባት የፀናች ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ ለማሻገር መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።
ዘጋቢ፡ ስንታየሁ ሙላቱ – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
የልማት መጓተትን ለማስቀረትና ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ በህብረት ተደጋግፎ መሥራት እንደሚገባ ተገለጸ
ከፋፋይ ከሆኑ አጀንዳዎች በመራቅ ህብረታችንን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ
በሀድያ ዞን ጎምቦራ ወረዳ ሀብቾ ከተማ ነዋሪ ለሆኑ አንዲት አቅመ ደካማ እናት የመኖሪያ ቤት ርክክብ ተደረገ