በበጀት አመቱ በ71 ሺህ 219 መዛግብት ላይ ውሳኔ መስጠት መቻሉ ተገለጸ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የ2018 በጀት አመት አፈፃፀም ለክልሉ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 6ኛ መደበኛ ጉበኤ ቀርቧል።
ሪፖርቱን ያቀረቡት የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ኤርሲኖ አቡሬ እንዳሉት፤ በበጀት አመቱ በ71 ሺህ 219 የወንጀልና የፍትሃብሄር መዛግብት ላይ ውሳኔ መስጠት ተችሏል።
በበጀት አመቱ ካለፈው አመት የተላለፈ የወንጀል 581 እና የፍትሐብሔር 1 ሺህ 469 በድምሩ 2 ሺህ 50 መዛግብት እንደቀረበ ገልፀዋል።
ፕሬዝደንቱ አያይዘውም በበጀት አመቱ አዲስ የቀረበው የፍትሐብሔር 44 ሺህ 845 የወንጀል 26 ሺህ 391 በድምሩ 73 ሺህ 217 መዛግብት እንደቀረበ በሪፖርታቸው አብራርተዋል።
በበጀት አመቱ ከቀረቡ 73 ሺህ 217 የወንጀልና የፍትሐብሔር መዛግብት ውስጥ በ71 ሺህ 219 መዛግብት ላይ ውሳኔ መስጠት መቻሉን አብራርተዋል።
ይህም ከባለፈው በጀት አመት ጋር ሲነፃፀር 3 በመቶ ብልጫ እንዳለው ፕሬዝዳንቱ ገልፀዋል።
ዘጋቢ፡ መለሰች ዘለቀ

More Stories
ለትምህርት ሥራ ስኬታማነት ባለድርሻ አካላት በቁርጠኝነትና በጋራ መስራት እንዳለባቸው ተገለፀ
የጉራጌ ማህበረሰብ ባህላዊ እሴቶች ሳይበረዙ ለትውልድ ለማስተላለፍ የኪነ ጥበብ ዘርፉን በማጠናከር ላይ እንደሚገኝ የጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ አስታወቀ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት 67 ቢሊየን ብር በጀት አጸደቀ