ችግኝ መትከል ጥሪት ለትውልድ የማስቀመጥ ተግባር  በመሆኑ ለተግባራዊነቱ በቅንጅት መረባረብ እንደሚገባ  የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ ሙስጠፋ ኢሳ ገለፁ።

ችግኝ መትከል ጥሪት ለትውልድ የማስቀመጥ ተግባር  በመሆኑ ለተግባራዊነቱ በቅንጅት መረባረብ እንደሚገባ  የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ ሙስጠፋ ኢሳ ገለፁ።

ሀገራዊ የ800 ሚሊየን ችግኝ በአንድ ጀምበር  ተከላ መርሀ ግብር በጉራጌ ዞን እዣ ወረዳ በያስሁራና ዋርቢያ ቀበሌ የዳምሳር ተፋሰስ  በመከናወን ላይ ይገኛል።

የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ ሙስጠፋ ኢሳ በመርሃ ግብሩ ላይ እንዳሉት “ችግኝ መትከል ጥሪት  ለትውልድ የማስቀመጥ ተግባር  በመሆኑ ለተግባራዊነቱ በቅንጅት መረባረብ ይገባል” ብለዋል።

በመርሃ ግብሩ የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ ሙስጠፋ ኢሳ፣ የጉራጌ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅሕፈት ቤት ሀላፊ አቶ ናስር ሀሰንን ጨምሮ ሌሎች የክልል፣ የዞን፣ የወረዳና ከተማ አስተዳደር የስራ ሀላፊዎች እና የቀበሌው የማህበረሰብ ክፍሎች ተሳትፈውበታል።

ዘጋቢ፣ አማረ መንገሻ – ከወልቂጤ ጣቢያችን