በኣሪ ዞን በባካ ዳዉላ ኣሪ ወረዳ “ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ቃል የአንድ ጀምበር አረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር እየተካሄደ ይገኛል

በኣሪ ዞን በባካ ዳዉላ ኣሪ ወረዳ “ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ቃል የአንድ ጀምበር አረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር እየተካሄደ ይገኛል

በወረዳዉ በሁሉም ቀበሌያት የዘንድሮዉ የአርንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ፕሮግራም እናቶች ፣ አባቶች ፣ወጣቶች ፣ሴቶች ህፃናት በአጠቃላይ ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የነገዋን ኢትዮጵያ አረንጓዴ አካባቢን ለመፍጠር በነቂስ በመውጣት የችግኝ ተከላ ፕሮግራም እያካሄዱ ነው።

በዘንድሮዉ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ እንደ ወረዳ ጠቅላላ ስድስት መቶ ሺህ (600,000)ችግኞች ይተከላሉ ተብሎም ይጠበቃል።

በመርሃ-ግብሩም ከክልል፣ከዞን እና የወረዳ አጠቃላይ አመራሮች ባለሙያዎች፣ተፅዕኖ ፈጣሪ ወጣቶች ነገ የሀገር ተረካቢ ህፃናት ባጠቃላይ ህብረተሰቡ እየተሳተፉም ነው።

ዘጋቢ፡ ተመስገን ሰይፉ – ከጂንካ ጣቢያችን