በኣሪ ዞን በባካ ዳዉላ ኣሪ ወረዳ “ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ቃል የአንድ ጀምበር አረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር እየተካሄደ ይገኛል
በወረዳዉ በሁሉም ቀበሌያት የዘንድሮዉ የአርንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ፕሮግራም እናቶች ፣ አባቶች ፣ወጣቶች ፣ሴቶች ህፃናት በአጠቃላይ ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የነገዋን ኢትዮጵያ አረንጓዴ አካባቢን ለመፍጠር በነቂስ በመውጣት የችግኝ ተከላ ፕሮግራም እያካሄዱ ነው።
በዘንድሮዉ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ እንደ ወረዳ ጠቅላላ ስድስት መቶ ሺህ (600,000)ችግኞች ይተከላሉ ተብሎም ይጠበቃል።
በመርሃ-ግብሩም ከክልል፣ከዞን እና የወረዳ አጠቃላይ አመራሮች ባለሙያዎች፣ተፅዕኖ ፈጣሪ ወጣቶች ነገ የሀገር ተረካቢ ህፃናት ባጠቃላይ ህብረተሰቡ እየተሳተፉም ነው።
ዘጋቢ፡ ተመስገን ሰይፉ – ከጂንካ ጣቢያችን
በኣሪ ዞን በባካ ዳዉላ ኣሪ ወረዳ “ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ቃል የአንድ ጀምበር አረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር እየተካሄደ ይገኛል

More Stories
እንደ ሀገር ”በጋራ ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ቃል በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል መርሃ-ግብር በሸካ ዞን በማሻ ማረሚያ ተቋም ተካሄደ
ችግኝ መትከል ጥሪት ለትውልድ የማስቀመጥ ተግባር በመሆኑ ለተግባራዊነቱ በቅንጅት መረባረብ እንደሚገባ የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ ሙስጠፋ ኢሳ ገለፁ።
በሀዋሳ ከተማም ከ220 ሺህ በላይ ችግኞችን በ8ቱም ክፍለ ከተሞች ”ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ቃል”እየተከለች ነው።