ከተረጂነት በመውጣት የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ የሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም መሸፈን እንደሚገባ ተገለጸ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ “ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለተሟላ ሀገራዊ ክብር እና ሉአላዊነት” በሚል መሪ ቃል የውይይት እና ከየቀበሌያት የተሰበሰቡ እህል እና ቁሳቁስ ለወረዳው አስተዳደር ገቢ ተደርገዋል።
ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በሚለው መርህ ትኩረት ተሰጥቶ በመሠራቱ ውጤታማ በመሆን ማህበረሰቡ ራሱን ችሎ ለሰብአዊ ድጋፍ የበኩሉን አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል።
በዞን ደረጃ ለመሰብሰብ አቅደን የጀመርነው 72 ሚሊዮን መጠባበቂያ ፈንድ በይርጋጨፌ ወረዳ በእህል እና በቁሳቁስ መልክ የተጀመረው የማሰባሰቡ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል ሲሉ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ(ዶ/ር) ተናግረዋል።
ይህም በሀገር አቀፍ ደረጃ ለተጀመረው ሥራ እያንዳንዱ አመራር ህብረተሰቡን በማንቀሳቀስና ትኩረት ሰጥቶ በመሥራት ተግባሩ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ማድረግ ይጠበቅበታል ብለዋል።
የይርጋጨፌ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ቡኔ፤ በወረዳው ባሉ ሁሉም ቀበሌያት ህብረተሰቡ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት የሚለውን ሀሳብ ተቀብሎ በመሥራት
አሁን ላይ ለሰብዓዊነት ከየቀበሌው እህል በመሰብሰብ በወረዳ ማዕከል የማስረከቡ ሥራ ተሠርቷል ሲሉ ተናግረዋል።
በቀጣይም በሰብአዊነት ራሳችንን ለመቻል የጀመርነውን ሥራ አጠናክረን ከማስቀጠልም ባሻገር በእያንዳንዱ ቀበሌ ያለው ማህበረሰብ ሠርቶ ምርታማ እንዲሆን በማድረግ ከተረጂነት መንፈስ ነፃ እና ራሱን የቻለ ማህበረሰብ መፍጠር ይኖርብናል ሲሉ ተናግረዋል።
ከተሳታፊዎች መካከል አርሶአደር አክሊሉ ወብዩ እና ጴጥሮስ በዳሶ፤ በቀበሌያቸው ከተረጂነት ለመውጣት በሚደረገው ጥረት ህብረተሰቡ የሚጠበቅበትን እህል በማዋጣት በወረዳ ደረጃ እንድናስረክብ ተደርጓል ብለዋል።
በመጪው ጊዜያትም ህብረተሰቡም ሆነ እኛ በግላችን ባለን ማሳ ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር ትኩረት ሰጥተን በመሥራት የሰብአዊ ድጋፉን እናስቀጥላለን ሲሉ አስረድተዋል።
ዘጋቢ፡ አብዶ አያላ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
ከተረጂነት በመውጣት የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ የሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም መሸፈን እንደሚገባ ተገለጸ

More Stories
ለህብረተሰቡ የላቀ የጤና አገልግሎት ተደራሽ በማድረግ በጤና ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶችን ከወረቀት ነፃ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ መሥራት እንደሚገባ ተገለጸ
በቀጣይ አወንታዊ ሙስናን የመከላከል ስትራቴጂ በመከተል ይሰራል ሲሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የስነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ማሞ ቴጋ ገለፁ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ትምህርት ቢሮ የ2019 የትምህርት ልማት ስራዎች የንቅናቄ መድረክ በታርጫ ከተማ እያካሄደ ነዉ