የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን አባላት በግብጽ አዲስ እየተገነባ ያለውን የካይሮ ከተማ ጎበኙ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 20/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን አባላት በግብጽ አዲስ እየተገነባ ያለውን የካይሮ ከተማ ጎብኝተዋል።
ከተለያዩ ከተሞች እና ተቋማት የተውጣጣው የልዑካን ቡድን የካይሮ ከተማን የሕዝብ ብዛት መጨናነቅ ለማስተንፈስ መልሶ የማልማት እና ለወደፊቱ ትውልድ የሚሆን ዘመናዊ፣ ሁለገብ እና ምቹ ከተማን ለመገንባት የተሠሩ ሥራዎችን ጎብኝቷል።
ጥንታዊነትን ከዘመናዊነት፤ ገጠርን ከከተማ አስማምቶ ለማደግ የተከናወኑ ተግባራትንም ተመልክቷል።
በጉብኝቱ ወቅት ከካይሮ ከተማ አስተዳደር ጋር ከተሞችን በማዘመን፣ ወቅቱን የዋጀ የከተማ እና የመሠረተ ልማት ግንባታን፣ እንዲሁም የተጨናነቁ የከተማ አካባቢዎችን ስለማስተካከል በተሰሩ ስራዎች ዙሪያ ውይይት ተካሂዷል።
ኢትዮጵያና ግብጽ በባህል፣ በታሪክና በሕዝብ ብዛት ተቀራራቢነት ያላቸው በመሆኑ የልዑካን ቡድኑ ያገኘው ልምድ በየከተሞቹ ሊተገበሩ የሚችሉ መሆናቸውን አባላቱ ገልጸዋል።
ጉብኝቱ ሐምሌ 6 ቀን 2015 ዓ.ም የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ በግብጽ ያደረጉትን ጉብኝት ተከትሎ የተከናወነ ነው።
በጉብኝቱ የፌደራል አመራሮች፣ የአዲስ አበባ፣ የአዳማ፣ የባሕር ዳርና የሐዋሳ ከንቲባዎችም ተሳትፈዋል።

More Stories
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ
የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) መጭው ጊዜ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ብርሃን የምንሸጋገርበት ብሩህ ዘመን መሆኑን ተናገሩ
በተቀሩት አጭር ቀናት ህብረተሠቡ የመራጭነት ካርዱን በመውሰድ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳና አካባቢው የፌደራልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጥሪ አቀረቡ