በኬሚካል ኢንዱስትሪ የጎማ ዛፍ ልማትና ፕሮጀክት አመራሮችና ሰራተኞች የአረንጓዴ አሻራ ተከላ መርሃ ግብር አካሄዱ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 19/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በኬሚካል ኢንዱስትሪ የጎማ ዛፍ ልማትና ፕሮጀክት አመራሮችና ሰራተኞች የአረንጓዴ አሻራ ተከላ መርሃ ግብር አካሂደዋል፡፡
የፕሮጀክቱ ተወካይ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዘማች ሳድንስ÷ ሃገር በቀልና የተለያዩ ጠቀሜታ ያላቸዉ ችግኞች መተከላቸዉን ገልፀዋል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የፕሮጀክቱ አመራሮችና ሰራተኞች የተሳተፉ ሲሆን በዕለቱም 2 ሺህ ችግኞችን መትከል መቻሉን አስረድተዋል።
ችግኞችን መትከል ለትዉልድ ቅርስን የማኖር ተግባር መሆኑን የገለፁት ኃላፊዉ የተተከሉትን ችግኞች የፅድቀት ደረጃን መከታተልና የመንከባከብ ተግባርም በትኩረት ይከናወናል ብለዋል።
በዕለቱ ካነጋገርናቸዉ የፕሮጀክቱ ሰራተኞች መካከል አቶ ታደሰ አባይነህ እና ወይዘሮ መረሃዊ ሀዱሽ በዚህ ታላቅ ሃገራዊ ጥሪ ላይ ተሳታፊ በመሆናቸዉ መደሰታቸዉን ገልፀዉ ቀጣይ ችግኞቹን በመንከባከብ የድርሻቸዉን እንደሚወጡ ገልፀዋል።
ዘጋቢ፡ ዮሐንስ አሰፋ – ከሚዛን ጣቢያችን
More Stories
በክረምት የተከናወኑ የወጣቶች በጎ ተግባራት ከ180 ሚሊየን ብር በላይ ከመንግስት ሊወጣ የነበረ ወጪ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የችሎት መዝገብ ስራ በቴክኖሎጂ የታገዘ በማድረግ የደንበኞቹን እርካታ ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ገለፀ
የፀጥታና የደህንነት ስጋቶችን በጋራ በመታገል ለሁለንተናዊ የሀገሪቱ ሠላም በቅንጅት ሊሰራ እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ካሳ ገለፁ