በኬሚካል ኢንዱስትሪ የጎማ ዛፍ ልማትና ፕሮጀክት አመራሮችና ሰራተኞች የአረንጓዴ አሻራ ተከላ መርሃ ግብር አካሄዱ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 19/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በኬሚካል ኢንዱስትሪ የጎማ ዛፍ ልማትና ፕሮጀክት አመራሮችና ሰራተኞች የአረንጓዴ አሻራ ተከላ መርሃ ግብር አካሂደዋል፡፡
የፕሮጀክቱ ተወካይ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዘማች ሳድንስ÷ ሃገር በቀልና የተለያዩ ጠቀሜታ ያላቸዉ ችግኞች መተከላቸዉን ገልፀዋል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የፕሮጀክቱ አመራሮችና ሰራተኞች የተሳተፉ ሲሆን በዕለቱም 2 ሺህ ችግኞችን መትከል መቻሉን አስረድተዋል።
ችግኞችን መትከል ለትዉልድ ቅርስን የማኖር ተግባር መሆኑን የገለፁት ኃላፊዉ የተተከሉትን ችግኞች የፅድቀት ደረጃን መከታተልና የመንከባከብ ተግባርም በትኩረት ይከናወናል ብለዋል።
በዕለቱ ካነጋገርናቸዉ የፕሮጀክቱ ሰራተኞች መካከል አቶ ታደሰ አባይነህ እና ወይዘሮ መረሃዊ ሀዱሽ በዚህ ታላቅ ሃገራዊ ጥሪ ላይ ተሳታፊ በመሆናቸዉ መደሰታቸዉን ገልፀዉ ቀጣይ ችግኞቹን በመንከባከብ የድርሻቸዉን እንደሚወጡ ገልፀዋል።
ዘጋቢ፡ ዮሐንስ አሰፋ – ከሚዛን ጣቢያችን

More Stories
“አንድነት የሚገነባው በውይይት ነው፤ ሰላም የሚጠናከረው በመግባባት ነው” ኢማም ሐጂ አብዱልሃዲ ሼክ አህመድ ቡርሃን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት
መደበኛ ባልሆነ መልኩ የሎተሪ ዕድል ሙከራን “ዕቁብ” በሚል ሽፋን በህገ-ወጥ ተግባር ላይ የተሳተፉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት አሳሰበ
መንግስት ባለፉት ጊዜያት በስርዓተ ትምህርት እና በመማር ማስተማር ሂደት የነበረውን ክፍተት ለመሙላት እያደረገ ያለውን እንቅስቃሴ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በጥናትና ምርምር የተደገፈ ስራ በመስራት መደገፍ እንደአለባቸው ተገለጸ