በጂንካ ዩኒቨርሲቲ የ12ኛ ክፍል ፈተና በሠላማዊ ሁኔታ እየተሠጠ ነው
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 19/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በጂንካ ዩኒቨርሲቲ ከ6 ሺ 600 በላይ ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ፈተና በሠላማዊ ሁኔታ እየወሰዱ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አስታወቀ፡፡
የዩኒቨርሲቲው የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር አለሙ ሀይላቴ ከተፈታኞቹ መካከል 89 የሚሆኑት ህፃን ይዘው የመጡ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
አንድ ነፍሰ ጡር ተማሪ በጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታል በሰላም የተገላገለች ሲሆን ፈተናውን በቀጣይ ዙር ትወስዳለች ተብሏል፡፡
የጂንካ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ኩሴ ጉድሼ ከፈተናው ጋር በተያያዘ ተቋሙ በቂ ዝግጅት አድርጎ ተማሪዎችን መቀበሉን አስታውቀዋል ።
እስከአሁን ድረስ ምንም ዓይነት ችግር አለመፈጠሩንም ተናግረዋል፡፡
ከትምህርት ሚኒስትር ፈተናውን ለማስተባበር ወደ ጂንካ ዩኒቨርስቲ የተመደቡት አቶ ፈቃዱ አሌ ከዘጠኝ ሺህ በላይ የተፈጥሮና ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ጂንካ ዩኒቨርስቲ ተመድበው የመጀመሪያ ዙር ተፈታኝ ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተናውን ሰላማዊ በሆነ መልኩ እየወሰዱ ይገኛሉ ብለዋል።
የዩኒቨርሲቲው ዝግጅት ጥሩ መሆኑንም ተመልክተናል ብለዋል አስተባባሪው፡፡
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ- ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
“አንድነታችንን በማጎልበት የህዝብ ጥቅም የሚያስቀድም ፖለቲካ ማራመድ ይጠበቅብናል” ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
የሕብረ-ብሔራዊ አንድነት መጠናከር መሰረት የሆነው ብዝሃነትን በአግባቡ የማስተናገድ ሂደት ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ያለው መሆኑ ተገለፀ
በክረምቱ ወራት ሊከሰቱ የሚችሉ የተለያዩ አደጋዎችን ለመከላከል አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ገለጸ