በጂንካ ዩኒቨርሲቲ የ12ኛ ክፍል ፈተና በሠላማዊ ሁኔታ እየተሠጠ ነው
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 19/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በጂንካ ዩኒቨርሲቲ ከ6 ሺ 600 በላይ ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ፈተና በሠላማዊ ሁኔታ እየወሰዱ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አስታወቀ፡፡
የዩኒቨርሲቲው የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር አለሙ ሀይላቴ ከተፈታኞቹ መካከል 89 የሚሆኑት ህፃን ይዘው የመጡ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
አንድ ነፍሰ ጡር ተማሪ በጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታል በሰላም የተገላገለች ሲሆን ፈተናውን በቀጣይ ዙር ትወስዳለች ተብሏል፡፡
የጂንካ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ኩሴ ጉድሼ ከፈተናው ጋር በተያያዘ ተቋሙ በቂ ዝግጅት አድርጎ ተማሪዎችን መቀበሉን አስታውቀዋል ።
እስከአሁን ድረስ ምንም ዓይነት ችግር አለመፈጠሩንም ተናግረዋል፡፡
ከትምህርት ሚኒስትር ፈተናውን ለማስተባበር ወደ ጂንካ ዩኒቨርስቲ የተመደቡት አቶ ፈቃዱ አሌ ከዘጠኝ ሺህ በላይ የተፈጥሮና ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ጂንካ ዩኒቨርስቲ ተመድበው የመጀመሪያ ዙር ተፈታኝ ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተናውን ሰላማዊ በሆነ መልኩ እየወሰዱ ይገኛሉ ብለዋል።
የዩኒቨርሲቲው ዝግጅት ጥሩ መሆኑንም ተመልክተናል ብለዋል አስተባባሪው፡፡
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ- ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ
የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) መጭው ጊዜ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ብርሃን የምንሸጋገርበት ብሩህ ዘመን መሆኑን ተናገሩ
በተቀሩት አጭር ቀናት ህብረተሠቡ የመራጭነት ካርዱን በመውሰድ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳና አካባቢው የፌደራልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጥሪ አቀረቡ