በጂንካ ዩኒቨርሲቲ የ12ኛ ክፍል ፈተና በሠላማዊ ሁኔታ እየተሠጠ ነው
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 19/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በጂንካ ዩኒቨርሲቲ ከ6 ሺ 600 በላይ ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ፈተና በሠላማዊ ሁኔታ እየወሰዱ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አስታወቀ፡፡
የዩኒቨርሲቲው የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር አለሙ ሀይላቴ ከተፈታኞቹ መካከል 89 የሚሆኑት ህፃን ይዘው የመጡ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
አንድ ነፍሰ ጡር ተማሪ በጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታል በሰላም የተገላገለች ሲሆን ፈተናውን በቀጣይ ዙር ትወስዳለች ተብሏል፡፡
የጂንካ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ኩሴ ጉድሼ ከፈተናው ጋር በተያያዘ ተቋሙ በቂ ዝግጅት አድርጎ ተማሪዎችን መቀበሉን አስታውቀዋል ።
እስከአሁን ድረስ ምንም ዓይነት ችግር አለመፈጠሩንም ተናግረዋል፡፡
ከትምህርት ሚኒስትር ፈተናውን ለማስተባበር ወደ ጂንካ ዩኒቨርስቲ የተመደቡት አቶ ፈቃዱ አሌ ከዘጠኝ ሺህ በላይ የተፈጥሮና ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ጂንካ ዩኒቨርስቲ ተመድበው የመጀመሪያ ዙር ተፈታኝ ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተናውን ሰላማዊ በሆነ መልኩ እየወሰዱ ይገኛሉ ብለዋል።
የዩኒቨርሲቲው ዝግጅት ጥሩ መሆኑንም ተመልክተናል ብለዋል አስተባባሪው፡፡
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ- ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
“አንድነት የሚገነባው በውይይት ነው፤ ሰላም የሚጠናከረው በመግባባት ነው” ኢማም ሐጂ አብዱልሃዲ ሼክ አህመድ ቡርሃን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት
መደበኛ ባልሆነ መልኩ የሎተሪ ዕድል ሙከራን “ዕቁብ” በሚል ሽፋን በህገ-ወጥ ተግባር ላይ የተሳተፉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት አሳሰበ
መንግስት ባለፉት ጊዜያት በስርዓተ ትምህርት እና በመማር ማስተማር ሂደት የነበረውን ክፍተት ለመሙላት እያደረገ ያለውን እንቅስቃሴ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በጥናትና ምርምር የተደገፈ ስራ በመስራት መደገፍ እንደአለባቸው ተገለጸ