በ2018 ከደረጃ “ለ” ከ13 ሺህ 300 ግብር ከፋዮች ከ80 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዷል – በሀላባ ዞን የቁሊቶ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 02/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በ2018 ከደረጃ “ለ” ከ13 ሺህ 300 ግብር ከፋዮች ከ80 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ አቅዶ ወደ ተግባር መግባቱን በሀላባ ዞን የቁሊቶ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት አስታወቀ::
የ2018 ማጠናቀቂያ የግብር መክፈያ መርሃ-ግብር በቁሊቶ ከተማ በ5 ማዕከላት በይፋ ተጀምሯል::
የከተማው ምክትል ከንቲባ እና ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብዱልቃድር ሎላሶ እንዳሉት፤ ገቢ የአንድ ሀገር ኢኮኖሚ መሠረት መሆኑን አመላክተው፥ በዚህም ለከተሞች ዕድገትና ሁለንተናዊ ልማት ጉልህ አበርክቶ አለው ብለዋል::
ግብር ከፋዮቹ ከትላንት ጀምሮ በሁሉም ማዕከላት ግብርን በአግባቡ እየከፈሉ መሆናቸውን ኃላፊው ጠቁመው፥ በዘንድሮው ዓመት ከደረጃ “ለ” 13ሺህ 300 ግብር ከፋዮች ከ80 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱንም አቶ አብዱልቃድር አስታውቀዋል::
ግብርን በወቅቱና በታማኝነት መክፈል ሀገራዊ ግዴታ መሆኑን በመገንዘብ ሁሉም ግብር ከፋይ ግዴታውን በመወጣት በከተማዋ ብሎም በሀገር ልማትና ዕድገት ላይ የድርሻውን አሻራ ሊያሳርፍ ይገባልም ብለዋል::
የከተማው ግብር ከፋዮችም ግብር ሀገራዊ ግዴታ መሆኑን በመገንዘብ በወቅቱና በታማኝነት እየከፈሉ ስለመሆናቸው ገልፀዋል::
ዘጋቢ፡ አብዱልሰመድ አወል – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የቀቤና ልዩ ወረዳ ማህበረሰብ የልማት ፍላጎት ማሟላት የሚቻለው ግብርና ታክስ በታማኝነትና በወቅቱ መክፈል ሲቻል መሆኑ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ የመንግሥትን ወጪና የልማት ፍላጎት ለመሸፈን በ2019 በጀት ዓመት 14 ቢሊየን ብር የሚጠጋ ገቢ ለመሰብሰብ ማቀዱን ገለጸ
በዞኑ ከ11ሺ 268 የደረጃ “ለ” ግብር ከፋዮች ከ56.8 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱ ተገለፀ