በ2018 ከደረጃ “ለ” ከ13 ሺህ 300 ግብር ከፋዮች ከ80 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዷል – በሀላባ ዞን የቁሊቶ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት

በ2018 ከደረጃ “ለ” ከ13 ሺህ 300 ግብር ከፋዮች ከ80 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዷል – በሀላባ ዞን የቁሊቶ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት

ሀዋሳ፡ ሐምሌ 02/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በ2018 ከደረጃ “ለ” ከ13 ሺህ 300 ግብር ከፋዮች ከ80 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ አቅዶ ወደ ተግባር መግባቱን በሀላባ ዞን የቁሊቶ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት አስታወቀ::

የ2018 ማጠናቀቂያ የግብር መክፈያ መርሃ-ግብር በቁሊቶ ከተማ በ5 ማዕከላት በይፋ ተጀምሯል::

የከተማው ምክትል ከንቲባ እና ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብዱልቃድር ሎላሶ እንዳሉት፤ ገቢ የአንድ ሀገር ኢኮኖሚ መሠረት መሆኑን አመላክተው፥ በዚህም ለከተሞች ዕድገትና ሁለንተናዊ ልማት ጉልህ አበርክቶ አለው ብለዋል::

ግብር ከፋዮቹ ከትላንት ጀምሮ በሁሉም ማዕከላት ግብርን በአግባቡ እየከፈሉ መሆናቸውን ኃላፊው ጠቁመው፥ በዘንድሮው ዓመት ከደረጃ “ለ” 13ሺህ 300 ግብር ከፋዮች ከ80 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱንም አቶ አብዱልቃድር አስታውቀዋል::

ግብርን በወቅቱና በታማኝነት መክፈል ሀገራዊ ግዴታ መሆኑን በመገንዘብ ሁሉም ግብር ከፋይ ግዴታውን በመወጣት በከተማዋ ብሎም በሀገር ልማትና ዕድገት ላይ የድርሻውን አሻራ ሊያሳርፍ ይገባልም ብለዋል::

የከተማው ግብር ከፋዮችም ግብር ሀገራዊ ግዴታ መሆኑን በመገንዘብ በወቅቱና በታማኝነት እየከፈሉ ስለመሆናቸው ገልፀዋል::

ዘጋቢ፡ አብዱልሰመድ አወል – ከሆሳዕና ጣቢያችን