በ2018 ከደረጃ “ለ” ከ13 ሺህ 300 ግብር ከፋዮች ከ80 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዷል – በሀላባ ዞን የቁሊቶ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 02/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በ2018 ከደረጃ “ለ” ከ13 ሺህ 300 ግብር ከፋዮች ከ80 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ አቅዶ ወደ ተግባር መግባቱን በሀላባ ዞን የቁሊቶ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት አስታወቀ::
የ2018 ማጠናቀቂያ የግብር መክፈያ መርሃ-ግብር በቁሊቶ ከተማ በ5 ማዕከላት በይፋ ተጀምሯል::
የከተማው ምክትል ከንቲባ እና ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብዱልቃድር ሎላሶ እንዳሉት፤ ገቢ የአንድ ሀገር ኢኮኖሚ መሠረት መሆኑን አመላክተው፥ በዚህም ለከተሞች ዕድገትና ሁለንተናዊ ልማት ጉልህ አበርክቶ አለው ብለዋል::
ግብር ከፋዮቹ ከትላንት ጀምሮ በሁሉም ማዕከላት ግብርን በአግባቡ እየከፈሉ መሆናቸውን ኃላፊው ጠቁመው፥ በዘንድሮው ዓመት ከደረጃ “ለ” 13ሺህ 300 ግብር ከፋዮች ከ80 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱንም አቶ አብዱልቃድር አስታውቀዋል::
ግብርን በወቅቱና በታማኝነት መክፈል ሀገራዊ ግዴታ መሆኑን በመገንዘብ ሁሉም ግብር ከፋይ ግዴታውን በመወጣት በከተማዋ ብሎም በሀገር ልማትና ዕድገት ላይ የድርሻውን አሻራ ሊያሳርፍ ይገባልም ብለዋል::
የከተማው ግብር ከፋዮችም ግብር ሀገራዊ ግዴታ መሆኑን በመገንዘብ በወቅቱና በታማኝነት እየከፈሉ ስለመሆናቸው ገልፀዋል::
ዘጋቢ፡ አብዱልሰመድ አወል – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
ምክር ቤቱ በ2018 በጀት አመት ሪፖርት እና የ2019 ጠቋሚ እቅድ ላይ ተወያይቶ በሙሉ ድምጽ አጸደቀ
በበጀት አመቱ ከ26 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰብስቧል – ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)
በበጀት ዓመቱ ከ379 ሺ በላይ ዜጎች የስራ እድል ተፈጥሮላቸዋል – ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)