በበጀት አመቱ 98ሺህ 200 ቶን የኢንዱትሪ ማእድንና 13ሺህ 110 ቶን ሜትር ኪዩብ የኮንስትራክሽን ማእድን ማምረት መቻሉ ተገለጸ

በበጀት አመቱ 98ሺህ 200 ቶን የኢንዱትሪ ማእድንና 13ሺህ 110 ቶን ሜትር ኪዩብ የኮንስትራክሽን ማእድን ማምረት መቻሉ ተገለጸ

ሀዋሳ፡ ሰኔ 26/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በበጀት አመቱ በማእድን ዘርፍ 98ሺህ 200 ቶን የኢንዱትሪ ማእድንና 13ሺህ 110 ቶን ሜትር ኪዩብ የኮንስትራክሽን ማእድን በማምረት ለኢንዱስትሪ ግብአት ማቅረብ መቻሉን የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ማእድንና ኢነርጂ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ መኮንን መኔዶ አስታወቁ።

ኤጀንሲው የ2018 በጀት አመት እቅድ አፈፃፀም ግምገማና የ2019 በጀት አመት እቅድ ላይ የሚመክር የውይይት መድረክ በወልቂጤ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።

የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ማእድንና ኢነርጂ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ መኮንን መኔዶ በዚህ ወቅት አንዳስታወቁት በበጀት አመቱ በማእድን ዘርፍ 98ሺህ 200 ቶን የኢንዱትሪ ማእድንና 13ሺህ 110 ቶን ሜትር ኪዩብ የኮንስትራክሽን ማእድን በማምረት ለኢንዱስትሪ ግብአት ማቅረብ መቻሉን ጠቁመው፥ በዘርፉ ከ9ሺህ 800 በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች የስራ እድል መፈጠሩን አስረድተዋል።

በምክክር መድረኩ ላይ የኤጀንሲው የ2018 እቅድ አፈፃፀምና በ2019 የቀጣይ የእቅድ አቅጣጫዎች ዙሪያ ውይይት ይደረጋል።

በመድረኩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የመሠረተ ልማት ጉዳዮች አማካሪ አቶ መዝረዲን ሁሴንን ጨምሮ በክልሉ ከሁሉም መዋቅሮች የተወጣጡ የዘርፉ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛሉ።

ዘጋቢ፡ አስቻለው ተስፋዬ – ከወልቂጤ ጣቢያችን