ሳንቲ ካዞርላ ከእግርኳስ ተጫዋችነት ራሱን አገለለ
የቀድሞ የአርሰናል አማካይ ሳንቲ ካዞርላ ከእግርኳስ ተጫዋችነት ራሱን ማግለሉን ይፋ አድርጓል።
25 ዓመታትን በተጫዋችነት ያሳለፈው ካዞርላ በ41 ዓመቱ ነው ራሱን ከእግርኳስ ተጫዋችነት ያገለለው።
ሳንቲ ካዞርላ በተጫዋችነት ዘመኑ በክለብ ደረጃ ለአርሰናል፣ማላጋ፣ቪያሪያልን፣ሪያል ኦቬዶ እና አል ሳድ ተጫውቶ አሳልፏል።
በብሔራዊ ቡድን ደረጃ ደግሞ ለስፔን 81 ጨዋታዎችን አከናውኖ 15 ጎሎችን በስሙ አስመዝግቧል። ሁለት የአውሮፓ ዋንጫዎችንም ከላሮጃዎች ጋር ማንሳት ችሏል።
ሳንቲ ካዞርላ ያለፉትን ሦስት ተከታታይ የውድድር ዓመታት በልጅነት ክለቡ ሪያል ኦቬዳ ሲጫወት መቆየቱ አይዘነጋም።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ
ሳንቲ ካዞርላ ከእግርኳስ ተጫዋችነት ራሱን አገለለ

More Stories
ማንቸስተር ሲቲ ኤሊዮት አንደርሰንን በይፋ አስፈረመ
ከጠጠር ሜዳ እስከ ፕሪሚየር ሊግ
ቼልሲ ማርኮ ፓሌስትራን አስፈረመ