ሳንቲ ካዞርላ ከእግርኳስ ተጫዋችነት ራሱን አገለለ
የቀድሞ የአርሰናል አማካይ ሳንቲ ካዞርላ ከእግርኳስ ተጫዋችነት ራሱን ማግለሉን ይፋ አድርጓል።
25 ዓመታትን በተጫዋችነት ያሳለፈው ካዞርላ በ41 ዓመቱ ነው ራሱን ከእግርኳስ ተጫዋችነት ያገለለው።
ሳንቲ ካዞርላ በተጫዋችነት ዘመኑ በክለብ ደረጃ ለአርሰናል፣ማላጋ፣ቪያሪያልን፣ሪያል ኦቬዶ እና አል ሳድ ተጫውቶ አሳልፏል።
በብሔራዊ ቡድን ደረጃ ደግሞ ለስፔን 81 ጨዋታዎችን አከናውኖ 15 ጎሎችን በስሙ አስመዝግቧል። ሁለት የአውሮፓ ዋንጫዎችንም ከላሮጃዎች ጋር ማንሳት ችሏል።
ሳንቲ ካዞርላ ያለፉትን ሦስት ተከታታይ የውድድር ዓመታት በልጅነት ክለቡ ሪያል ኦቬዳ ሲጫወት መቆየቱ አይዘነጋም።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ
ሳንቲ ካዞርላ ከእግርኳስ ተጫዋችነት ራሱን አገለለ

More Stories
ማንቸስተር ዩናይትድ ግብ ጠባቂ አስፈረመ
ማንቸስተር ዩናይትድ አንድሬ ሳንቶስን አስፈረመ
የ2018 የCBE የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ እና የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪሚየር ሊግ ውድድርን በማሸነፍ ሁለት ዋንጫ ላነሳው የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ክልሉ ያዘጋጀውን የዕውቅናና የሽልማት ፕሮግራም ዛሬ ሰኞ ሐምሌ 06/2018 ከቀኑ 12፡00 ጀምሮ በሀዋሳ ሀይሌ ሪዞርት ይካሄዳል።