በክልሉ በመስኖ ልማት ዘርፍ ቀጣይነት ያለው ዕድገት ማስመዝገብ እንዲቻል ስትራቴጂካዊ አቅድ ተነድፎ እየተሰራ ነው
ሀዋሳ፡ ሰኔ 25/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በክልሉ በመስኖ ልማት ዘርፍ ቀጣይነት ያለው ዕድገት ማስመዝገብ እንዲቻል ስትራቴጂካዊ አቅድ ተነድፎ እየተሰራ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመስኖ ተቋማት ልማትና አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ካሳዬ ተክሌ(ኢ/ር) ገለፁ፡፡
ኤጀንሲው በአማካሪው ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የቀረበውን የክልሉን የመስኖ አቅም ስትራቴጂ ጥናት የባለድርሻ አካላት በተገኙበት በወልቂጤ ከተማ እየገመገመ ይገኛል።
ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመስኖ ተቋማት ልማትና አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ካሳዬ ተክሌ(ኢ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት እንደ ሀገር ብሎም እንደ ክልል በመስኖ ልማት ዘርፍ በዘመናዊ መንገድ ብዙ እንዳልተሰራ አስታውሰው ከለውጡ በኋላ ግን ብዙ ጥረቶች እንዳሉ አመላክተዋል።
በዚህም በክልሉ በመስኖ ልማት ዘርፍ ቀጣይነት ያለው ዕድገት ማስመዝገብ እንዲቻል ስትራቴጂካዊ አቅድ ተነድፎ እየተሰራ ነው።
የኦሞ ጊቤ ተፋሰስና በሪፍት ቫሊ የተደረገ ጥናት ቢኖርም በክልሉ በአስሩም መዋቅሮች ላይ በሁሉም መስክ በመሬቱም፣ በውሃ ሀብቱ ለመስኖ ልማት የሚውለውን አቅም ለመለየት አስቸጋር እንደነበረ ጠቅሰው፥ ይህንን ችግር ለመቅረፍ ከሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ጋር ውል በመግባት ጥናት ሲደረግ እንደነበር ዋና ዳይሬክተሩ አንስተዋል።
በዛሬው ዕለት በዝርዝር የሚቀረቡ የጥናት ውጤቶች ላይ ሳይንሳዊና ሙያዊ ሀሳብ መስጠት ለማዳበር የሚያስችል ዓላማ ያደረገ መድረክ መሆኑንም አመላክተዋል።
በምክክር መድረኩ ላይ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የርዕሰ መስተዳድሩ የመሠረተ ልማት ጉዳዮች አማካሪ አቶ መዝረዲን ሁሴን፣ የክልሉ የማዕድንና ኢኔርጂ ልማት ኤጂንሲ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ መኮንን መኔዶን ጨምሮ የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ መምህርና የጥናት ቡድኑ መሪ ፕሮፈሰር አለማየሁ ሙሉነህና ሌሎች በጥናቱ ላይ የተሳተፉ ምሁራን እና እንዲሁም ከዞንና ከልዩ ወረዳ የተውጣጡ የዘርፉ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ዘጋቢ፡ ተዘራ በቀለ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
የምርጥ ዘር ችግርን መቅረፍና ማልማት የሚያስችል 1 ሺህ ሄክታር መሬት ከኣሪ ዞን ርክክብ ተካሄደ
የሚተከሉ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ መርሐ ግብሮች የአየር ሚዛንን ከማስጠበቅ ባሻገር በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ተገለጸ
በክልሉ 295 የቱሪዝም መዳረሻዎችን በመለየት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ