የጋሞ ዞን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የምርጫ ካርድ የመጣል ሂደት መጠናቀቁን ተከትሎ መግለጫ ሰጡ
ምክር ቤቱ የቅድመ-ምርጫ፣ የምርጫ ወቅትና የድህረ-ምርጫ ሥራዎችን በዝርዝር ከገመገመ በኋላ ነው ወቅታዊ አቋሙን ይፋ ያደረገው።
የምክር ቤቱ ሰብሳቢ መምህር ቴዎድሮስ ፋንታዬ እና ምክትል ሰብሳቢው አቶ ተመስገን እዩኤል የጋራ አቋማቸውን በገለጹበት ወቅት፤ ማህበረሰቡ በነቂስ ወጥቶ፣ በሰላም ካርዱን ጥሎ ያለምንም የጸጥታ ችግር ወደ ቤቱ መመለሱን አንስተዋል።
በሂደቱ ላይ የተስተዋሉ ማናቸውም ቅሬታዎች የምርጫው ህግ በሚፈቅደው መሠረት ብቻ ምላሽ ማግኘት አለባቸውም ተብሏል።
ምክር ቤቱ ይፋዊ የምርጫ ውጤት በይፋ እስኪገለጽ ድረስ መላው ህብረተሰብ የተለመደውን የዲሞክራሲ ባህል በማሳየት በትዕግስት መጠበቅ ይኖርበታል ብለዋል።
የጋራ ምክር ቤቱ ፈታኙን የአየር ንብረት ተቋቁሞ፣ የዜግነት ግዴታውን በሰላማዊ መንገድ ለተወጣውና ለሂደቱ ስኬት ዋነኛ ባለቤት ለሆነው መላው ማህበረሰብ የላቀ ምስጋና አቅርቧል።
ዘጋቢ : አማሮ አርሳባ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን
የጋሞ ዞን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የምርጫ ካርድ የመጣል ሂደት መጠናቀቁን ተከትሎ መግለጫ ሰጡ

More Stories
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላም ለመጠናቀቁ የመላው የክልሉ ህዝብ ተሳትፎ ላቅ ያለ ድርሻ ማበርከቱን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋር ምክር ቤት ገለፀ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውሃ፣ መስኖና ማዕድን ልማት ቢሮ በዋን ዋሽ ፕሮግራም አማካኝነት ከ1 መቶ 15 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ 4 የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ግንባታ ለማከናወን የውል ስምምነት ተፈራረመ
በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመታገዝ በዝንጅብል ምርት የተሰማሩ አርሶ አደሮች ተጠቃሚ መሆናቸውን ገለፁ