የጋሞ ዞን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የምርጫ ካርድ የመጣል ሂደት መጠናቀቁን ተከትሎ መግለጫ ሰጡ
ምክር ቤቱ የቅድመ-ምርጫ፣ የምርጫ ወቅትና የድህረ-ምርጫ ሥራዎችን በዝርዝር ከገመገመ በኋላ ነው ወቅታዊ አቋሙን ይፋ ያደረገው።
የምክር ቤቱ ሰብሳቢ መምህር ቴዎድሮስ ፋንታዬ እና ምክትል ሰብሳቢው አቶ ተመስገን እዩኤል የጋራ አቋማቸውን በገለጹበት ወቅት፤ ማህበረሰቡ በነቂስ ወጥቶ፣ በሰላም ካርዱን ጥሎ ያለምንም የጸጥታ ችግር ወደ ቤቱ መመለሱን አንስተዋል።
በሂደቱ ላይ የተስተዋሉ ማናቸውም ቅሬታዎች የምርጫው ህግ በሚፈቅደው መሠረት ብቻ ምላሽ ማግኘት አለባቸውም ተብሏል።
ምክር ቤቱ ይፋዊ የምርጫ ውጤት በይፋ እስኪገለጽ ድረስ መላው ህብረተሰብ የተለመደውን የዲሞክራሲ ባህል በማሳየት በትዕግስት መጠበቅ ይኖርበታል ብለዋል።
የጋራ ምክር ቤቱ ፈታኙን የአየር ንብረት ተቋቁሞ፣ የዜግነት ግዴታውን በሰላማዊ መንገድ ለተወጣውና ለሂደቱ ስኬት ዋነኛ ባለቤት ለሆነው መላው ማህበረሰብ የላቀ ምስጋና አቅርቧል።
ዘጋቢ : አማሮ አርሳባ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን
የጋሞ ዞን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የምርጫ ካርድ የመጣል ሂደት መጠናቀቁን ተከትሎ መግለጫ ሰጡ

More Stories
“አንድነት የሚገነባው በውይይት ነው፤ ሰላም የሚጠናከረው በመግባባት ነው” ኢማም ሐጂ አብዱልሃዲ ሼክ አህመድ ቡርሃን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት
መደበኛ ባልሆነ መልኩ የሎተሪ ዕድል ሙከራን “ዕቁብ” በሚል ሽፋን በህገ-ወጥ ተግባር ላይ የተሳተፉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት አሳሰበ
መንግስት ባለፉት ጊዜያት በስርዓተ ትምህርት እና በመማር ማስተማር ሂደት የነበረውን ክፍተት ለመሙላት እያደረገ ያለውን እንቅስቃሴ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በጥናትና ምርምር የተደገፈ ስራ በመስራት መደገፍ እንደአለባቸው ተገለጸ