ሊቨርፑል አሰልጣኝ አርኔ ስሎትን አሰናበተ
የመርሲሳይዱ ክለብ ሊቨርፑል ዋና አሰልጣኙን አርኔ ስሎት ከሀላፊነት ማሰናበቱን አሳውቋል።
ሆላንዳዊው አሰልጣኝ አርኔ ስሎት ሊቨርፑልን በተረከቡበት ባለፈው የውድድር ዘመን ክለቡን ለ20ኛ ጊዜ የሊጉ ሻምፒዮን እንዲሆን ቢያስችሉም ዘንድሮ ባስመዘገቡት ደካማ ውጤት ከሀላፊነታቸው ተነስተዋል።
ሊቨርፑል በዘንድሮው የውድድር በሁሉም ውድድሮች በ19 ጨዋታዎች ተሸንፎ በሊጉ 5ኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁ ይታወቃል።
አሰልጣኝ ዩርገን ክሎፕን ተክተው እንግሊዝ የደረሱት የ47 ዓመቱ አሰልጣኝ አርኔ ስሎት ሁለት ዓመታትን ብቻ በሊቨርፑል ቆይተው ነው የተሰናበቱት።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ሲዳማ ቡና አዳማ ከተማን በማሸነፍ መሪነቱን አጠናከረ
የጋብሪኤል ጄሱስ የወደፊት ዕጣ ፈንታ
ማንቸስተር ዩናይትድ የአታላንታውን አማካይ ኤደርሰንን ለማስፈረም ተቃረበ