ሲዳማ ቡና ኢትዮጵያ መድህንን በማሸነፍ ወደ ፍፃሜ አለፈ
በኢትዮጵያ ዋንጫ ግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ሲዳማ ቡና የወቅቱን የሊጉ ሻምፒዮን ኢትዮጵያ መድህንን በመለያ ምት በማሸነፍ ወደ ፍፃሜ አልፏል።
በአዲስ አበባ አበበ ቢቂላ ስታዲየም የተካሄደው የሁለቱ ክለቦች መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ 2 አቻ በሆነ ውጤት ተጠናቋል።
በጨዋታ ለሲዳማ ቡና መስፍን ታፈሰ እና ያሬድ ባየህ (በፍፁም ቅጣት) ሲያስቆጥሩ ለኢትዮጵያ መድህን አማኑኤል ኤርቦ አስቆጥሯል።
አሸናፊውን ለመለየት በተሰጠው የመለያ ፍፁም ቅጣት ምት ሲዳማ ቡና 4ለ3 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ዓመት ለፍፃሜ ደርሷል።
በፍፃሜው የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ጋር የሚጫወት ይሆናል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ከቪዬራ እስከ ኦዴጋርድ
መሐመድ ሳላህ ከአንፊልድ ሲሰናበት
“ አርሰናልን መቀላቀሌ ትክክለኛ ውሳኔ ነበር ” ዴክላን ራይስ