የብልጽግና ፓርቲ በርካታ ችግሮችን አስወግዶ የሚጨበጥ ተስፋና ነገን በብቃት ለመተለም የሚያስችል ራዕይ ሰንቆ እየሰራ እንዳለ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) ገለጹ
የብልጽግና ፓርቲ ዞናዊ የማጠቃለያ የምርጫ ቅስቀሳውን በጌዴኦ ዞን ዲላ ከተማ አካሂዷል።
የዲላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መስፍን ደምሴ (ዶ/ር) የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ባደረጉበት ወቅት፤ ብልጽግና ፓርቲ ሀገር ሲረከብ የነበሩ በርካታ ችግሮችን በማስተካከል ዛሬ ላይ በርካታ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ስኬቶች ተመዝግበዋል ብለዋል።
የዲላ ከተማ ወደ ሪጂዮ ፖሊስ ከተማ ያደገችበት ነው ያሉት መስፍን ደምሴ(ዶ/ር)፤ ከተማዋን ወደ ስማርት ሲቲ የመቀየርና ከ2 መቶ 53 በላይ ፕሮጀክቶች መሰራታቸውን ተናግረዋል።
በንጹህ የመጠጥ ውሃ፣ በጤና፣ በትምህርት፣ በገቢ አሰባሰብና ስራ ፈጠራ የተለያዩ ስራዎች መሰራታቸውን ገልጸዋል።
የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ(ዶ/ር) ባለፉት አምስት አመታት ብልጽግና ፓርቲ በውስብስብ ችግሮች ውስጥ እያለፈ ሀገርን በጠንካራ የተባበሩ ክንዶች እያሸጋገረ መሆኑን አመላክተዋል።
ፓርቲው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ካሉ ሀገራት በኢኮኖሚ ወደ ከፍተኛ ደረጃ እንድትመጣ አስችሏል ያሉት ዶ/ር ዝናቡ፤ የስንዴ ልማታችን በምግብ ሰብል ራስን ከመቻል ባለፈ የሀገር ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ አስችሏል ብለዋል።
ባለፉት አመታት በዞኑ በቡና ልማትና ግብይት በእንሰት ልማት ኢኒሼቲቭ እንዲሁም በምግብ ራስን መቻል የተለያዩ ስራዎች ተሰርተው ውጤታማ መሆን መቻላቸውን ዶ/ር ዝናቡ ተናግረዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ(ዶ/ር)፤ የብልጽግና ፓርቲ የሉዐላዊነትና የአንድነት አለመጣጣም፣ ስር የሰደደ ድህነት፣ አውዳሚ ግጭትና ጦርነት፣ ዴሞክራሲያዊ የሆነ ስርዓት አለመኖርና የመሳሰሉ ችግሮችን አስወግዶ የሚጨበጥ ተስፋና ነገን በብቃት ለመተለም የሚያስችል ራዕይ ሰንቆ እየሰራ እንዳለ ገልጸዋል።
በፓርቲው መሪነት ለአመታት የተጓተቱ ፕሮጀክቶችን ከማጠናቀቅ ባለፈ የበጋ ስንዴና የሌማት ትሩፋት፣ በግብርና ምርትና ምርታማነት በማሳደግ በምግብ ሰብል ራሳችንን የመቻል ሁኔታን እያረጋገጥን እንገኛለን ሲሉ ዶ/ር አበባየሁ ተናግረዋል።
በሰላም ግንባታ፣ የተመጣጠነ ምግብ፣ ንጹህ የመጠጥ ውሃ፣ ፍትሐዊ የጤና እንክብካቤ ዜጎች እንዲያገኙ እንደሚሰሩ የተናገሩት ዶ/ር አበባየሁ፤ የትውልድ ልህቀትን ለማረጋገጥ የመምህራንን ህይወትና ጥቅማቸውን ለማሻሻል ፓርቲው ከመቼውም ጊዜ በበለጠ እንደሚሰራ ጠቁመዋል።
በድጋፍ ሰልፉ ከተገኙት መካከል መቅደስ ክፍሌና አቡሽ ሙንጣዝ፤ ሰላማዊ ምርጫ በማድረግ መንግስትን ማስቀጠል እንደሚገባ ተናግረዋል።
ዘጋቢ: ውብሸት ካሳሁን – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
የብልጽግና ፓርቲ በርካታ ችግሮችን አስወግዶ የሚጨበጥ ተስፋና ነገን በብቃት ለመተለም የሚያስችል ራዕይ ሰንቆ እየሰራ እንዳለ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) ገለጹ

More Stories
እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል አድሐ በዓል አደረሰን፣ አደረሳችሁ! – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
55ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ውሳኔዎች
ግንቦት 24 የሚካሄደውን ጠቅላላ ምርጫን ምከንያት በማድረግ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በኣሪ ዞን ጂንካ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች የድጋፍ ሰልፍ አካሄዱ