በ25 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባው የማሪ ቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል በርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) መርቀው የከፈቱት የግብይት ማዕከሉ በ25 ሚሊየን ብር ወጪ ተገንብቶ የተጠናቀቀ እንደሆነ ተገልጿል።
ግንባታው በ11 ወራት ጊዜ ውስጥ የተጠናቀቀ መሆኑ ተጠቁሟል።
በዳውሮ ዞን የማሪ አካባቢ ከፍተኛ የቁም እንስሳት ግብይት የሚፈፀምበት በመሆኑ የግብይት ማዕከሉ ግንባታ የግብይት ሂደትን ከማቀላጠፍ በተጨማሪ ለገቢ አሰባሰብ ሂደት ቅልጥፍናን ይፈጥራል ተብሏል።
ከ10 ሺህ 2 መቶ በላይ ካሬ ሜትር ላይ ያረፈው የግብይት ማዕከሉ የእንስሳት መገበያያ፣ ከማዕከሉ ተገዝተው ወደሌላ ቦታ ለሚወሰዱ እንስሳት ወደ መኪና መጫኛ ቦታ፣ የታመሙ እንስሳት ተለይተው የሚቆዩበት ህክምና ቦታን አካቶ የተሠራ ነው።
ዘጋቢ፡ ዮሐንስ መካሻ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
በከምባታ ዞን ሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርአት (E-LMIS) ምዝገባ በይፋ መጀመሩን የከተማው ኢንተርፕራይዝና ሥራ ዕድል ፈጠራ ጽህፈት ቤት አስታወቀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በተከሰተው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ተደረገ
ህብረተሰቡ የኤሌክትሪክ መስመሮችን ጨምሮ ለእሳት አደጋ መንስኤ የሚሆኑ የመጠቀሚያ ዕቃዎችን በጥንቃቄ በመጠቀም በሰው ህይወት እና ንብረት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት መከላከል እንደሚገባ ተገለጸ