በ25 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባው የማሪ ቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል በርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) መርቀው የከፈቱት የግብይት ማዕከሉ በ25 ሚሊየን ብር ወጪ ተገንብቶ የተጠናቀቀ እንደሆነ ተገልጿል።
ግንባታው በ11 ወራት ጊዜ ውስጥ የተጠናቀቀ መሆኑ ተጠቁሟል።
በዳውሮ ዞን የማሪ አካባቢ ከፍተኛ የቁም እንስሳት ግብይት የሚፈፀምበት በመሆኑ የግብይት ማዕከሉ ግንባታ የግብይት ሂደትን ከማቀላጠፍ በተጨማሪ ለገቢ አሰባሰብ ሂደት ቅልጥፍናን ይፈጥራል ተብሏል።
ከ10 ሺህ 2 መቶ በላይ ካሬ ሜትር ላይ ያረፈው የግብይት ማዕከሉ የእንስሳት መገበያያ፣ ከማዕከሉ ተገዝተው ወደሌላ ቦታ ለሚወሰዱ እንስሳት ወደ መኪና መጫኛ ቦታ፣ የታመሙ እንስሳት ተለይተው የሚቆዩበት ህክምና ቦታን አካቶ የተሠራ ነው።
ዘጋቢ፡ ዮሐንስ መካሻ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት አባል በመሆናቸው ከድንገተኛ ህክምና ወጪ መዳን እንዳስቻላቸው ተገልጋዮች ገለጹ
ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ የኢሠራ ባሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል መሠረተ ድንጋይ አስቀምጧል
3ኛው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የክለቦች ሻምፒዮና የምድብ ድልድል ይፋ ሆነ