በ25 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባው የማሪ ቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል በርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) መርቀው የከፈቱት የግብይት ማዕከሉ በ25 ሚሊየን ብር ወጪ ተገንብቶ የተጠናቀቀ እንደሆነ ተገልጿል።
ግንባታው በ11 ወራት ጊዜ ውስጥ የተጠናቀቀ መሆኑ ተጠቁሟል።
በዳውሮ ዞን የማሪ አካባቢ ከፍተኛ የቁም እንስሳት ግብይት የሚፈፀምበት በመሆኑ የግብይት ማዕከሉ ግንባታ የግብይት ሂደትን ከማቀላጠፍ በተጨማሪ ለገቢ አሰባሰብ ሂደት ቅልጥፍናን ይፈጥራል ተብሏል።
ከ10 ሺህ 2 መቶ በላይ ካሬ ሜትር ላይ ያረፈው የግብይት ማዕከሉ የእንስሳት መገበያያ፣ ከማዕከሉ ተገዝተው ወደሌላ ቦታ ለሚወሰዱ እንስሳት ወደ መኪና መጫኛ ቦታ፣ የታመሙ እንስሳት ተለይተው የሚቆዩበት ህክምና ቦታን አካቶ የተሠራ ነው።
ዘጋቢ፡ ዮሐንስ መካሻ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
“አስቶን ቪላን ብወደውም ዩናይትድ ታላቅ ክለብ ነው” ዩሪ ቲሌማንስ
የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ የ2018 ዓ.ም የክረምት ወራት የትምህርት ቅድመ ዝግጅት ስራዎች ግምገማ እና የ2019 ዓ.ም የተማሪዎች ቅበላ የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው
የዳውሮ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 13ኛ ሥራ ዘመን 29ኛ መደበኛ ጉባዔ መካሄድ ጀመረ