ለሰባተኛ ጠቅላላ ምርጫ ሴት እጩዋችን የማስተዋወቅ መድረክ በወላይታ ሶዶ ከተማ እየተካሄደ ነዉ

ለሰባተኛ ጠቅላላ ምርጫ ሴት እጩዋችን የማስተዋወቅ መድረክ በወላይታ ሶዶ ከተማ እየተካሄደ ነዉ

ሀዋሳ፡ ሚያዚያ 20/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ቤት የሴቶች ክንፍ የድጋፍ ስልፍ እና ለሰባተኛዉ ሀገራዊ ምርጫ ሴት እጩዋችን የማስተዋወቅ መድረክ በወላይታ ሶዶ ከተማ እየተካሄደ ነዉ፡፡

በመርሀ-ግብሩ በ7ኛ ጠቅላላ ምርጫ ብልፅግና ፓርቲን በመወከል ለክልልና ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረቡ ዕጩዎች ትዉዉቅ የሚካሄድ ይሆናል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገብረ መስቀል ጫላን ጨምሮ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም የፓርቲው ሴት አባላት በሰልፉ ተሳታፌ ሆነዋል።

ዘጋቢ፡ ባዬሽ ጉልላት