ሲዳማ ቡና መቀሌ 70 እንደርታን በማሸነፍ መሪነቱን አጠናከረ

ሲዳማ ቡና መቀሌ 70 እንደርታን በማሸነፍ መሪነቱን አጠናከረ

በ25ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ ሲዳማ ቡና መቀሌ 70 እንደርታን 1ለ0 በማሸነፍ መሪነቱን አጠናክሯል።

ከአመሻሽ 12 ሰዓት ጀምሮ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አቤል ያለው ለሲዳማ ቡና ወሳኟን የማሸነፊያ ጎል አስገኝቷል።

አቤል ያለው በሲዳማ ቡና ማልያ ሦስተኛ የሊግ ጎሉን ነው ያስቆጠረው።

በበጋው የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ሲዳማ ቡናን የተቀላቀለው አቤል ያለው በውድድር ዘመኑ አጠቃላይ 11ኛ የሊግ ጎሉን በማስቆጠር ከፍተኛ ግብ አግቢነቱን እየመራ ይገኛል።

በአሰልጣኝ ያሬድ ገመቹ የሚመራው ሲዳማ ቡና በውድድር ዓመቱ 13ኛ የሊግ ድሉን አስመዝግቧል።

ሲዳማ ቡና ማሸነፉን ተከትሎ ነጥቡን 48 በማድረስ ከተከታዩ ሀዋሳ ከተማ በ8 ነጥብ ርቆ ሊጉን ይመራል።

መቀሌ 70 እንደርታ በአንፃሩ በ23 ነጥብ 19ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

ዘጋቢ ፡ ሙሉቀን ባሳ