አርሰናል የክርስቲያን ኮፋኔን የዝውውር ሁኔታ መከታተል ጀመረ
የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል የባየር ሌቨርኩሰኑን ወጣት አጥቂ ክርስቲያን ኮፋኔን የዝውውር ሁኔታ መከታተል መጀመሩ ተዘግቧል።
ኮፋኔ ከሳምንታት በፊት በተካሄደው በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ሌቨርኩሰን በመድፈኞቹ በድምር ውጤት 3ለ1 በተረታበት ጨዋታ አስደናቂ ብቃቱን ማሳየቱ ይታወሳል።
አሁን ላይ አርሰናል የ19 ዓመቱን ተጫዋች የዝውውር ሁኔታ ማጥናት መጀመሩን ስካይ ጀርመኒ አስነብቧል።
በዘንድሮው የውድድር ዘመን ካሜሩናዊ አጥቂ ክርስቲያን ኮፋኔ በጀርመኑ ክለብ እያሳየ ባለው ብቃት ምክንያት ከአርሰናል በተጨማሪ ሌሎች ትልልቅ የአውሮፓ ክለቦች ለማስፈረም ፍላጎት እያሳዩ መሆኑን መረጃዎች ይጠቁማሉ።
ባየር ሌቨርኩሰን ከተጫዋቾቹ ዝውውር ከ60 እስከ 70 ሚሊዮን ዩሮ የዝውውር ሒሳብ እንደሚፈልግ ተመላክቷል።
ክርስቲያን ኮፋኔ በዚህ ለባየር ሌቨርኩሰን በሁሉም ውድድሮች 39 ጨዋታዎችን ያከናወነ ሲሆን 7 ጎሎችን አስቆጥሮ 8 ጎል የሆኑ የመጨረሻ ኳሶችን አመቻችቶ አቀብሏል።
ዘጋቢ፡ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ፈረንሳይ ስፔንን በመብለጥ በወቅታዊ የሀገራት ደረጃ ቀዳሚ ሆነች
ስፖርት ህዝባዊ መሠራት እንዲኖረው ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ ቀረበ
የጎፋ ዞን የ2018 ዓ.ም ልዩ ልዩ የስፖርት ሻምፒዮና ውድድር እየተካሄደ ነው