በአፍሪካ ዋንጫ የተሳታፊ ሀገራት ቁጥር ላይ ጭማሪ ተደረገ
ሀዋሳ፡ መጋቢት 21/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) ከቀጣዩ የ2027 የአፍሪካ ዋንጫ ጀምሮ የተሳታፊ ሀገራት ቁጥር ላይ ጭማሪ መደረጉን ካፍ አሳውቋል።
የካፍ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት በትናንትናው ዕለት በግብፅ ካይሮ ባደረጉት ስብሰባ የተሳታፊ ሀገራት ቁጥር ከ24 ወደ 28 ሀገራት እንዲያድግ መወሰኑ ተገልጿል።
የ2027 የአፍሪካ ዋንጫ በሦስቱ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ኬንያ፣ታንዛኒያ እና ኡጋንዳ የጣምራ አዘጋጅነት እንደሚካሄድ ይታወቃል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ስፖርት ህዝባዊ መሠራት እንዲኖረው ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ ቀረበ
የጎፋ ዞን የ2018 ዓ.ም ልዩ ልዩ የስፖርት ሻምፒዮና ውድድር እየተካሄደ ነው
አሰልጣኝ ኢጎር ቱዶር ከ44 ቀናት ቆይታ በኋላ ቶትንሃምን ለቀቁ