ሁሉም ሰው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በቀጣይ የሚያስተዳድረውን መንግስት መምረጥ እንዲችል የምርጫ ካርድ በወቅቱ መያዝ እንደሚጠበቅበት ተገለጸ
የጎፋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊና በዑባ ደብረ ጸሐይ ምርጫ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዕጩ ተወካይ አቶ ጋሻያለሁ ገላ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በሚወዳደሩበት ምርጫ ክልል ካርድ በወሰዱበት ጊዜ እንደገለጹት ሁሉም ሰው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በቀጣይ የሚያስተዳድረውን መንግስት መምረጥ እንዲችል የምርጫ ካርድ መያዝ ይጠበቅበታል።
የ7ኛ ሀገራዊ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ በዞኑ በሚገኙ ስድስት የምርጫ ክልሎች በሚገኙ 351 የምርጫ ጣቢያዎች ተጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን ባለው ቀሪ የምዝገባ ጊዜ ዕድሜው ለመራጭነት የደረሰ ዜጋ ሁሉ አሻራውን በማኖር ህገ መንግስታዊ መብቱን እንዲጠቀም አስገንዝበዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ልዩ አማካሪና የዑባ ደብረፀሐይ የምርጫ ክልል የክልል ምክር ቤት ዕጩ ተወካይ ዶ/ር ቦሻ ቦምቤ በበኩላቸው፥ የዘንድሮ ምርጫ በአይነቱ የተለየና የዴሞክራሲ ምህዳሩን በማስፋት ሁሉንም ማህበረሰብ ተሳታፊ ያደረገ መሆኑን ገልፀዋል።
በዘንድሮ ምርጫ ሁሉም ዜጋ ተሳታፊ መሆን ይጠበቃል ያሉት ዶክተር ቦሻ፥ ምርጫው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን በክልሉ መንግስት በቂ ዝግጅት መደረጉን ጠቁመዋል።
ምርጫ መንግስት የሚመሰረትበት ብቸኛ መንገድ በመሆኑ ዜጎች የመምረጥ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ ጠይቀዋል።
ዘጋቢ፡ አይናለም ሰለሞን – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል