በ7ኛ ጠቅላላ ምርጫ ላይ ለመሳተፍ ሁሉም ዜጋ የምርጫ ካርድ መያዝ እንደሚገባው ተገለጸ
ሀዋሳ፡ መጋቢት 18/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በመጪው ግንቦት ወር በሚደረገው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ በመራጭነት ለመሳተፍ ሁሉም ዜጋ የምርጫ ካርድ መያዝ እንደሚገባው በባስኬቶ ዞን የሚንቀሳቀሱ ተወዳዳሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ።
የዘንድሮ ምርጫ ሁሉም ፓርቲዎች በነፃነት የሚሳተፉበት፣ ነጻና ገለልተኛ የፖለቲካ ምህዳር የታየበት መሆኑን በዞኑ የሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጠቁመዋል።
በባስኬቶ ዞን በ7ኛ ጠቅላላ ምርጫ ለክልልና ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውክልና የሚወዳደሩ በርካታ ፓርቲዎች መካከል ብልጽግና፣ ኢዜማና ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ፓርቲ ተጠቃሽ ናቸው።
ከፓርቲዎቹ አባላትና ዕጩዎች መካከል አንዳዶቹ እንደገለጹልን የምርጫ ቦርድ ባስቀመጠው የጊዜ ገደብ መሠረት በወቅቱ ተመዝግቦ የምርጫ ካርድ መውሰድ ህገ መንግስታዊ መብትን በአግባቡ መጠቀም መሆኑን አስረድተዋል።
ሁሉም ዕድሜው ለምርጫ የደረሰ የትኛውም የዞኑ ነዋሪ በጊዜ ተመዝግቦ የምርጫ ካርዱን እንዲይዝም ጥሪ አቅርበዋል።
ዘጋቢ: አወል ከድር – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ