በ7ኛ ጠቅላላ ምርጫ ላይ ለመሳተፍ ሁሉም ዜጋ የምርጫ ካርድ መያዝ እንደሚገባው ተገለጸ

በ7ኛ ጠቅላላ ምርጫ ላይ ለመሳተፍ ሁሉም ዜጋ የምርጫ ካርድ መያዝ እንደሚገባው ተገለጸ

ሀዋሳ፡ መጋቢት 18/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በመጪው ግንቦት ወር በሚደረገው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ በመራጭነት ለመሳተፍ ሁሉም ዜጋ የምርጫ ካርድ መያዝ እንደሚገባው በባስኬቶ ዞን የሚንቀሳቀሱ ተወዳዳሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ።

የዘንድሮ ምርጫ ሁሉም ፓርቲዎች በነፃነት የሚሳተፉበት፣ ነጻና ገለልተኛ የፖለቲካ ምህዳር የታየበት መሆኑን በዞኑ የሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጠቁመዋል።

በባስኬቶ ዞን በ7ኛ ጠቅላላ ምርጫ ለክልልና ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውክልና የሚወዳደሩ በርካታ ፓርቲዎች መካከል ብልጽግና፣ ኢዜማና ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ፓርቲ ተጠቃሽ ናቸው።

ከፓርቲዎቹ አባላትና ዕጩዎች መካከል አንዳዶቹ እንደገለጹልን የምርጫ ቦርድ ባስቀመጠው የጊዜ ገደብ መሠረት በወቅቱ ተመዝግቦ የምርጫ ካርድ መውሰድ ህገ መንግስታዊ መብትን በአግባቡ መጠቀም መሆኑን አስረድተዋል።

ሁሉም ዕድሜው ለምርጫ የደረሰ የትኛውም የዞኑ ነዋሪ በጊዜ ተመዝግቦ የምርጫ ካርዱን እንዲይዝም ጥሪ አቅርበዋል።

ዘጋቢ: አወል ከድር – ከሳውላ ጣቢያችን