የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ለማሳለጥ የሚጠበቅባቸውን ግብር በወቅቱና በታማኝነት እንደሚከፍሉ አንዳንድ የአርባምንጭ ከተማ ነጋዴዎች ተናግረዋል።
አንዳንድ የአርባምንጭ ከተማ ነጋዴዎች፤ የአርባምንጭ ከተማን ዕድገት ለመደገፍ እና የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ከዳር ለማድረስ የሚጠበቅባቸውን ግብር በወቅቱ በመክፈል ግዴታቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል።
በግብር አሰባሰብ ሂደት የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን በማረምና ወቅቱን የጠበቀ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት በቀጣይ መሰጠት እንደሚጠበቅ ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።
የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ በረከት ማቲዮስ፤ በ2018 በጀት አመት በ5 ወራት ውስጥ 1 ቢሊየን 5 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉንና የተያዘውን እቅድ ለማሳካት የተለያዩ ተግዳሮቶች እንደነበሩ አስረድተዋል።
አቶ በረከት አክለውም፤ ከአዲሱ የገቢ ግብር አሰባሰብ ጋር በተያያዘ በግብር አከፋፈል ላይ የሚስተዋሉ የግንዛቤ ክፍተቶችን ለመቅረፍ መስሪያ ቤቱ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርቶችን እየሰጠ እንደሆነም ጠቁመዋል።
የግብር ስወራን ለመከላከልና ተገቢዉን ግብር በወቅቱ ባልከፈሉት ግብር ከፋዮች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃዎች እየተወሰዱ እንደሆነም አስታውቀዋል።
የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ለማሳለጥ ሁሉንም የገቢ ግብር ርዕሶችን አሟጦ በመጠቀም የገቢ መጠንን በማሳደግ ረገድ ሰፊ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመዋል።
በተቋሙና በግብር ከፋዩ ዘንድ የበለጠ ቅንጅታዊ አሰራርን ለመዘርጋት እየተሰራ እንደሆነም አቶ በረከት ገልጸዋል።
ዘጋቢ፡ ስምረት አስማማው – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል