የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር ጋር በመመተባበር የቃል ኪዳን ቤተሰብ ምስረታ አካሂዷል።
የጋሞ አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች መርሃ-ግብሩን በምርቃት ያስጀመሩ ሲሆን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ኢ/ር አብደላ ከማል የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ፕሬዝዳንቱ በንግግራቸው የቃል ኪዳን ቤተሰብ ምስረታ ዓላማ በአርባምንጭ ከተማ ማህበረሰብና ተማሪዎች መካከል ጥብቅ ግንኙነት በመፍጠር በትምህርትና ስልጠና የበቁ ዜጎችን መፍጠር ነው ብለዋል።
የአርባምንጭ ከተማ ከንቲባ ዶ/ር መስፍን መንዛ በመርሃ-ግብሩ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ተግባሩ ትልቅ ሀላፊነት በመሆኑ በጋራ እንወጠዋለን ብለው ህብረ ብሔራዊ አንድነትን የሚያጠናክር ስምምነት እንደሆነም ገልፀዋል።
የሠላም ሚኒስቴር ተወካይ ወ/ሮ ዮዲት ከበደ የሠላም ዋጋ የላቀ ስለሆነ ዘላቂ ሠላም ለማምጣት የቃል ኪዳን ቤተሰብ ትስስር የላቀ ፋይዳ መኖሩን ተናግረዋል።
በልጆች ላይ ዛሬ የሚዘራው ዘር ነገ በመልካም ጤንነትና ውጤት እንዲመለሱ ከማድረጉም በላይ የተጠማነውን ሠላም ለማግኘት ይረዳል ብለዋል።
በዩኒቨርሲቲው ፖለቲካል ሳይንስ መምህር የሆኑት ተፈራ ቃኛለው በማህበረሰቡና ተማሪዎች መካከል ጥልቅ ትስስር በማስፈን እና ምቹ የሆነ የትምህርት እና ስልጠና ከባቢ በመፍጠር ውጤታማ የሆኑ ተማሪዎችን ማፍለቅ የፕሮግራሙ ዋና ዓላማ እንደሆነ አብራርተዋል።
ከቃል ኪዳን ተማሪዎች መካከል ቤተልሄም ባልቻ መርሃ -ግብሩ በዩኒቨርስቲው በመጀመሩ መደሰቷን ተናግራ ለአንድነትና ለሠላም ትልቅ ጥቅም ይኖረዋል ነው ያለችው።
ከቃል ኪዳን ቤተሰብ መካከል ዶ/ር ተክሉ ወጋየሁ በተቀበሉት ሀላፊነት ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረው የተጣለባቸውን ኃላፊነት በፍፁም ቅንነት እንደሚወጡ ገልፀዋል።
ወላጅና ቤተሰብ በመጣመር ውል ከተፈራረሙ በኃላ መርሃ-ግብሩ በብሔራዊ መዝሙር መቋጫውን አግኝቷል።
ዘጋቢ: ተነሳ ተረፈ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የሴቶችና ህፃናት ጥቃት ለመከላከል ቅድሚያ ከራስ መጀመር እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ኤርሲኖ አቡሬ ገለፁ
በተለያዩ የልማት መስኮች ሴቶችን በማሳተፍ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑ ተመላከተ
“ከጂኦ ስትራቴጂካዊ ኩስምና ወደ ታደሰ ቁመና” በሚል መሪ ቃል የካፋ ዞን ፖሊስ መምሪያ አመራር አባላት የስልጠና መድረክ ተጀመረ