የብልጽግና ፓርቲ 3ኛው ዙር ስልጠና አካል የሆነው የመስክ ጉብኝት በዲላ ከተማ ተካሂዷል
የዲላ ከተማ አስተዳደር መካከለኛ አመራሮች በከተማው በማኑፋክቸሪንግ፣ በከተማ ግብርና፣ በቱሪዝም እና በሌሎች ዘርፎች እየተመዘገቡ ያሉ እምርታዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡
የጉብኝቱ ዓላማ መንግሥት የህዝቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፍላጎቶችን በአግባቡ ለመመለስ እያደረገ ያለውን ጥረት ማሳየትና እምርታውን ለማስቀጠል በቁጭት የመሥራት ሞራልን ከፍ ለማድረግ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
ጉብኝቱ የከተማውን የግበርና፣ የማኑፋክቸሪንግና የከተማ ልማት እምርታዎችን ጨምሮ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የእፅዋት ጥበቃና ኢኮ ቱሪዝም ማዕከልን ያካተተ መሆኑ ነው የተገለፀው፡፡
ጉብኝቱ የፓርቲው መካከለኛ አመራሮች ፀጋን ለይቶ በማልማት ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ እንደሚቻል በተግባር እንዲመለከቱ ያስቻለና በትብብር ከተሰራ ሁለንተናዊ እምርታን ማስመዝገብ እንደሚቻል ተጨባጭ ማሳያ መሆኑን የስልጠናው ተሳታፊ አመራሮች አስረድተዋል።
የብልጽግና ፓርቲ የ2018 ዓ.ም ዓመታዊ የመካከለኛ አመራር ስልጠና “በመደመር መንግሥት እይታ፤ የዘርፎች እምርታ” በሚል መሪ ቃል በዲላ ከተማ እየተሰጠ ይገኛል።
ዘጋቢ፡ ሳሙኤል በቀለ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
የብልጽግና ፓርቲ 3ኛው ዙር ስልጠና አካል የሆነው የመስክ ጉብኝት በዲላ ከተማ ተካሂዷል

More Stories
ሠላምን በሠላም ጊዜ እንደሚሠራ ተገለጸ
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሴንተር ፎር ኢምፓወርመንት ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በጎፋ ዞን ለሲቪክ ማህበራት ስልጠና ሰጠ
የሃይማኖት ተቋማት ፅንፈኝነትን፣ አክራርነትንና ከፋፋይ አጀንዳዎችን በመጠየፍ ሰላምና አንድነትን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ ተገለጸ