20ኛውን የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን ምክንያት በማድረግ የኢትዮጵያዊያን የምክክር ቀን መካሄድ ጀመረ
ሀዋሳ: ሕዳር 28/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) “ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሄራዊ አንድነት ” በሚል መሪ ቃል የሚከበረው 20ኛውን የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን ምክንያት በማድረግ የኢትዮጵያዊያን የምክክር ቀን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ እየተካሔደ ነው።
20ኛውን የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን ምክንያት በማድረግ የሚካሄደው “የኢትዮጵያዊያን የምክክር ቀን” በርካታ እንግዶች በተገኙበት በመካሄድ ላይ ነው።
በሲምፖዚየሙ ላይ የኢፌዴሪ ፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)፣ የክልሉ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ፣ የክልሉ ብሄረሰቦች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ፣ የክልል ርዕሰ መስተዳድሮች፣ ምሁራን፣ የሀይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች የባህል አምባሳደሮችና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት በመካሄድ ላይ ነው።
ዘጋቢ: ዘላለም ተስፋዬ

More Stories
የፍትህ ዘርፍ ባለሙያዎችን አቅም ማጎልበት በፍትህ ስርዓት ላይ የሚነሱ ችግሮችን እንደሚቀርፍ ተጠቆመ
በስራ ቦታቸው ላይ የህፃናት ማቆያ ማዕከል መቋቋሙ ስራቸውን በአግባቡ ለማከናወን እንዳስቻላቸው የማእከሉ ተጠቃሚ እናቶች ገለፁ
ለግብርናው እድገት መንግስት ከሚያደርገው ጥረት ጎን ለጎን የግብርና አጋር አካላት ድጋፍ የማይተካ ሚና እንዳለው የጎፋ ዞን ግብርና መምሪያ ገለጸ