የ20ኛዉ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን ክልላዊ የማጠቃለያ ፕሮግራም በሳጃ ከተማ እደተካሄደ ነዉ
ሀዋሳ፡ ሕዳር 22/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የ20ኛዉ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን ክልላዊ የማጠቃለያ ፕሮግራም የክልሉ አንዱ ብዝሃ የክልሉ ማዕከል በሆነዉ በየም ዞን ሳጃ ከተማ እደተካሄደ ነዉ።
“ዴሞክራሲያዊ መግባባት፤ ለኅብረብሔራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል የሚከበረዉ የ20ኛዉ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በፌደሬሽን ምክር ቤት አስተባባሪነትና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አስተናጋጅነት የሚከበር ሲሆን በዓሉ በቀጣይ ቀናት በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ህዳር 29 በሆሳዕና ከተማ ሀገር አቀፍ ማጠቃለያ ይደርጋል፡፡
በክልላዊ ማጠቃለያ ፕሮግራሙ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ (ዶ/ር)፣ የክልሉ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ሰርሞሎ፣ የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ፣ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ኤርሲኖ አቡሬን ጨምሮ ሌሎች አመራሮችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ድልነሳው ታደሰ

More Stories
በከምባታ ዞን ሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርአት (E-LMIS) ምዝገባ በይፋ መጀመሩን የከተማው ኢንተርፕራይዝና ሥራ ዕድል ፈጠራ ጽህፈት ቤት አስታወቀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በተከሰተው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ተደረገ
ህብረተሰቡ የኤሌክትሪክ መስመሮችን ጨምሮ ለእሳት አደጋ መንስኤ የሚሆኑ የመጠቀሚያ ዕቃዎችን በጥንቃቄ በመጠቀም በሰው ህይወት እና ንብረት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት መከላከል እንደሚገባ ተገለጸ