“ዲሞክራሲያዊ መግባባት፤ ለህብረብሄራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል በሀላባ ዞን 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ እየተከበረ ይገኛል።
ህገ-መንግስቱ የኢትዮጵያ ፀጋ የሆነውን ብዝሀነት እንዲከበር፣ መብቶች እንዲከበሩ፣ ህብረ ብሔራዊ አንድነት እንዲጎለብትና በመፈቃቀድ ላይ የተመሰረተ ኀብረ ብሔራዊ አንድነት ስር እንዲሰድ ያስቻለ በመሆኑ የሚያጋጥሙ ጥቃቅን የሆኑ ልዩነቶችን በዲሞክራሲያዊ መግባባት መፍታት ያስፈልጋል ተብሏል።
በመርሀ-ግብሩ ላይ የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙህዲን ሁሴን፣ የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊና የዞኑ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ መሀመደከማል ኑሪዬ፣ የዞኑ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ፣ የዞን፣ የከተማ አስተዳደርና ወረዳዎች አመራሮች እና የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።
ምንጭ፡ የዞኑ የመንግስት ኮሙኒኬሽን

More Stories
በዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ የጥምቀት በዓል በተለያዩ ሀይማኖታዊ ክዋኔዎች በድምቀት ተከብሯል
የ1447ኛው ዓመተ ሂጅራ የሀጅ ምዝገባ ጥር 18 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ የሲዳማ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት አስታወቀ
በኮንታ ዞን አመያ ከተማ የጥምቀት በዓል በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል