“ዲሞክራሲያዊ መግባባት፤ ለህብረብሄራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል በሀላባ ዞን 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ እየተከበረ ይገኛል።
ህገ-መንግስቱ የኢትዮጵያ ፀጋ የሆነውን ብዝሀነት እንዲከበር፣ መብቶች እንዲከበሩ፣ ህብረ ብሔራዊ አንድነት እንዲጎለብትና በመፈቃቀድ ላይ የተመሰረተ ኀብረ ብሔራዊ አንድነት ስር እንዲሰድ ያስቻለ በመሆኑ የሚያጋጥሙ ጥቃቅን የሆኑ ልዩነቶችን በዲሞክራሲያዊ መግባባት መፍታት ያስፈልጋል ተብሏል።
በመርሀ-ግብሩ ላይ የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙህዲን ሁሴን፣ የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊና የዞኑ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ መሀመደከማል ኑሪዬ፣ የዞኑ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ፣ የዞን፣ የከተማ አስተዳደርና ወረዳዎች አመራሮች እና የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።
ምንጭ፡ የዞኑ የመንግስት ኮሙኒኬሽን

More Stories
በከምባታ ዞን ሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርአት (E-LMIS) ምዝገባ በይፋ መጀመሩን የከተማው ኢንተርፕራይዝና ሥራ ዕድል ፈጠራ ጽህፈት ቤት አስታወቀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በተከሰተው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ተደረገ
ህብረተሰቡ የኤሌክትሪክ መስመሮችን ጨምሮ ለእሳት አደጋ መንስኤ የሚሆኑ የመጠቀሚያ ዕቃዎችን በጥንቃቄ በመጠቀም በሰው ህይወት እና ንብረት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት መከላከል እንደሚገባ ተገለጸ