“ዲሞክራሲያዊ መግባባት፤ ለህብረብሄራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል በሀላባ ዞን 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ እየተከበረ ይገኛል።
ህገ-መንግስቱ የኢትዮጵያ ፀጋ የሆነውን ብዝሀነት እንዲከበር፣ መብቶች እንዲከበሩ፣ ህብረ ብሔራዊ አንድነት እንዲጎለብትና በመፈቃቀድ ላይ የተመሰረተ ኀብረ ብሔራዊ አንድነት ስር እንዲሰድ ያስቻለ በመሆኑ የሚያጋጥሙ ጥቃቅን የሆኑ ልዩነቶችን በዲሞክራሲያዊ መግባባት መፍታት ያስፈልጋል ተብሏል።
በመርሀ-ግብሩ ላይ የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙህዲን ሁሴን፣ የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊና የዞኑ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ መሀመደከማል ኑሪዬ፣ የዞኑ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ፣ የዞን፣ የከተማ አስተዳደርና ወረዳዎች አመራሮች እና የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።
ምንጭ፡ የዞኑ የመንግስት ኮሙኒኬሽን

More Stories
በሀሬ ተፋሰስበ በ27 ቀናት ወስጥ 35 ሄክታር መሬት ላይ እርከን ፣ አፈር እቀባና የተለያዩ ዕፅዋት ተከላ መከናወኑ ተገለፀ
አዲሱ የቦንጋ ከተማ መዋቅራዊ ፕላን የኡፋ እና የውሽውሽ ከተሞችን ያካተተ መሆኑን በሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የከተማ ልማት ዲን አቶ ደጉ በቀለ ገለጹ
የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በየዓመቱ ህዳር 29 ቀን እንዲከበር ሲወሰን ዓላማው ብሔር ብሔረሰቦች ባህሎቻቸውን በመለዋወጥ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጠናከር ሃገራዊ መግባባትን እንዲፈጥሩ ማድረግ ነው – የኢፌዴሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር