20ኛው የብሔር ብሔረሰቦች ቀን በዓል ዞናዊ ማጠቃለያ በተለያዩ መረሀግብሮች በወልቂጤ ከተማ እየተከበረ ነው
ሀዋሳ፡ ሕዳር 20/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) “ዴሞክራሲያዊ መግባባት፤ ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል የሚከበረው 20ኛው የብሔር ብሔረሰቦች ቀን በዓል ዞናዊ ማጠቃለያ በተለያዩ መረሀግብሮች በወልቂጤ ከተማ እየተከበረ ይገኛል።
በዞናዊ የማጠቃለያ መርሃ ግብር ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ፤ ለ20ኛ የብሔር ብሔረሰቦች ቀን በዓል የእንኳን አደረሰን መልክት አስተላልፈዋል።
በመልዕክታቸውም በዓሉ የኢትዮጵያ ህዝቦች በዓል በመሆኑ የሁሉም ብሄር ብሄረሰቦች ባህል ቋንቋና ሌሎችም እሴቶችን ለማስተዋወቅ እንዲሁም የህዝብ ለህዝብ ትስስር ለማጠናከር ፋይዳው የጎላ በመሆኑ ለተግባሩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
የጉራጌ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ኸይሩ መሀመድ፤ “ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል የሚከበረው 20ኛው የብሔር ብሔረሰቦች ቀን በዓል ዞናዊ ማጠቃለያ በሁሉም የዞን መዋቅሮች ከህዳር አንድ ጀምሮ ሲከበር ቆይቶ ዛሬ እንደዞን ከወልቂጤና አበሽጌ ወረዳ አስተዳደሮች በትብብር የማጠቃለያ መርሃ ግብር እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል።
በመርሃ ግብሩ የጉራጌ ዞን የአበሽጌ ወረዳና የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አባላት ተገኝተው ወታደራዊ የሰልፍ ትርዒት ያቀረቡ ሲሆን በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችና የወልቂጤ ከተማ ነዋሪዎች የተለያዩ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን አከናውነዋል።
በመድረኩ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ፣ የዞኑ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ኸይሩ መሀመድ፣ የዞኑ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አለማየሁ ገ/መስቀልን ጨምሮ ሌሎችም የክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደሩ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ አማረ መንገሻ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
በሀሬ ተፋሰስበ በ27 ቀናት ወስጥ 35 ሄክታር መሬት ላይ እርከን ፣ አፈር እቀባና የተለያዩ ዕፅዋት ተከላ መከናወኑ ተገለፀ
አዲሱ የቦንጋ ከተማ መዋቅራዊ ፕላን የኡፋ እና የውሽውሽ ከተሞችን ያካተተ መሆኑን በሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የከተማ ልማት ዲን አቶ ደጉ በቀለ ገለጹ
የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በየዓመቱ ህዳር 29 ቀን እንዲከበር ሲወሰን ዓላማው ብሔር ብሔረሰቦች ባህሎቻቸውን በመለዋወጥ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጠናከር ሃገራዊ መግባባትን እንዲፈጥሩ ማድረግ ነው – የኢፌዴሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር