በብልጽግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት 2ኛ ዙር ሰልጣኝ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች በቀቤና ልዩ ወረዳ በመስኖ ልማት እየተከናወኑ ያሉ የግብርና ስራዎችንና የቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎችን እየጎበኙ ነው
በብልጽግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት 2ኛ ዙር የከፍተኛና መካከለኛ አመራር ስልጠና የአመራሩን አቅም በሚገነቡ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሰሞኑን በክልል ደረጃ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑ ይታወቃል።
የቀቤና ልዩ ወረዳ 2ኛ ዙር ሰልጣኝ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮችም ከስልጠናዉ በተጓዳኝ በልዩ ወረዳው በሩሙጋና በደቀንሺሞላ በመስኖ እየተከናወኑ ያሉ የተለያዩ የልማት ስራዎችንና የቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎችን የመስክ ጉብኝት እያካሄዱ ይገኛሉ፡፡
በልዩ ወረዳው በመስኖ እየለማ ያለው መሬትና የተሳታፊ አርሶ አደሮች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱ የተገለፀ ሲሆን በዕለቱ በልዩ ወረዳው በሩሙጋ ቀበሌ በ32 ሄክታር መሬት በክላስተር እየለማ ያለ የሽንኩርት ሰብል ተጎብኝቷል፡፡
በጉብኝቱ ላይ የክልሉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ወ/ሮ መነቴ ሙንዲኖ እንዲሁም የክልሉ ማዕድንና ኢነርጂ ኤጀንሲ ኃላፊ አቶ መኮንን መኔዶ፣ የልዩ ወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ አሚን በደዊ፣ የልዩ ወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ካፉ አረቦን ጨምሮ ሌሎችም የልዩ ወረዳው ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ፡፡
ዘጋቢ፡ ጅላሉ ፈድሉ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
በከምባታ ዞን ሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርአት (E-LMIS) ምዝገባ በይፋ መጀመሩን የከተማው ኢንተርፕራይዝና ሥራ ዕድል ፈጠራ ጽህፈት ቤት አስታወቀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በተከሰተው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ተደረገ
ህብረተሰቡ የኤሌክትሪክ መስመሮችን ጨምሮ ለእሳት አደጋ መንስኤ የሚሆኑ የመጠቀሚያ ዕቃዎችን በጥንቃቄ በመጠቀም በሰው ህይወት እና ንብረት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት መከላከል እንደሚገባ ተገለጸ