‎የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ በሽታ ስርጭትን ለመግታት የተያዘውን ዕቅድ ከግብ ለማድረስ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ ጥሪ አቀረበ

‎የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ በሽታ ስርጭትን ለመግታት የተያዘውን ዕቅድ ከግብ ለማድረስ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ ጥሪ አቀረበ

‎የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ የኤች.አይ.ቪ/ኤድስና ጉበት በሽታ መከላከያና መቆጣጠር ዘርፍ አስተባባሪ አቶ ዳዊት ፈይሳ በህብረተሰቡ ዘንድ በተፈጠረው መዘናጋት የቫይረሱ ስርጭት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

‎የበሽታው ስርጭት እየጨመረ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ዳዊት፤ ይህን ለመግታት የተያዘውን ዕቅድ ከግብ ለማድረስ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበቀዋል፡፡

‎በትምህርት ቤቶች፣ በሀይማኖት ተቋማት፣ በገበያ ስፍራዎችና በህዝብ መገኛ ስፍራዎች ስለበሽታው አስከፊነት ግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት በመስጠት የበሽታውን ስርጭት ለመቀነስ እየሠሩ መሆናቸውን የገለጹት በመምሪያው የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ በሽታ መከላከል ባለሙያ አቶ አሸናፊ ብርሃኑ ናቸው፡፡

‎አልኮል አብዝቶ ባለመጠቀም፣ ልቅ ከሆነ ግብረ ስጋ ግንኙነት በመታቀብና ለበሽታው አጋላጭ ከሆኑት ነገሮች እራስን በማቀብ ስርጭቱን ለመግታት የተያዘውን ዕቅድ ከግብ ለማድረስ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ አቶ አሸናፊ አሳስበዋል፡፡


‎ዘጋቢ፡ ውብሸት ኃ/ማርያም – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን