የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ በሽታ ስርጭትን ለመግታት የተያዘውን ዕቅድ ከግብ ለማድረስ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ ጥሪ አቀረበ
የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ የኤች.አይ.ቪ/ኤድስና ጉበት በሽታ መከላከያና መቆጣጠር ዘርፍ አስተባባሪ አቶ ዳዊት ፈይሳ በህብረተሰቡ ዘንድ በተፈጠረው መዘናጋት የቫይረሱ ስርጭት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የበሽታው ስርጭት እየጨመረ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ዳዊት፤ ይህን ለመግታት የተያዘውን ዕቅድ ከግብ ለማድረስ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበቀዋል፡፡
በትምህርት ቤቶች፣ በሀይማኖት ተቋማት፣ በገበያ ስፍራዎችና በህዝብ መገኛ ስፍራዎች ስለበሽታው አስከፊነት ግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት በመስጠት የበሽታውን ስርጭት ለመቀነስ እየሠሩ መሆናቸውን የገለጹት በመምሪያው የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ በሽታ መከላከል ባለሙያ አቶ አሸናፊ ብርሃኑ ናቸው፡፡
አልኮል አብዝቶ ባለመጠቀም፣ ልቅ ከሆነ ግብረ ስጋ ግንኙነት በመታቀብና ለበሽታው አጋላጭ ከሆኑት ነገሮች እራስን በማቀብ ስርጭቱን ለመግታት የተያዘውን ዕቅድ ከግብ ለማድረስ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ አቶ አሸናፊ አሳስበዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ውብሸት ኃ/ማርያም – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ በሽታ ስርጭትን ለመግታት የተያዘውን ዕቅድ ከግብ ለማድረስ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ ጥሪ አቀረበ

More Stories
በመንግስት ድጋፍና በህብረተሰቡ ተሣትፎ የተገነባው ጤና ጣቢያ በጎፋ ዞን ደንባ ጎፋ ወረዳ ወይዴ ውርኪ ማዕከል ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
የሳውላ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ወንጀልን የሚጸየፉ አምራች ዜጎችን ለማፍራት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገለፀ
በዳውሮ ዞን ገና ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የምረጡኝ ቅስቀሳና የፓርቲ ምርጫ ምልክት የማስተዋወቅ መርሃ ግብር ተካሄደ