የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ በሽታ ስርጭትን ለመግታት የተያዘውን ዕቅድ ከግብ ለማድረስ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ ጥሪ አቀረበ
የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ የኤች.አይ.ቪ/ኤድስና ጉበት በሽታ መከላከያና መቆጣጠር ዘርፍ አስተባባሪ አቶ ዳዊት ፈይሳ በህብረተሰቡ ዘንድ በተፈጠረው መዘናጋት የቫይረሱ ስርጭት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የበሽታው ስርጭት እየጨመረ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ዳዊት፤ ይህን ለመግታት የተያዘውን ዕቅድ ከግብ ለማድረስ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበቀዋል፡፡
በትምህርት ቤቶች፣ በሀይማኖት ተቋማት፣ በገበያ ስፍራዎችና በህዝብ መገኛ ስፍራዎች ስለበሽታው አስከፊነት ግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት በመስጠት የበሽታውን ስርጭት ለመቀነስ እየሠሩ መሆናቸውን የገለጹት በመምሪያው የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ በሽታ መከላከል ባለሙያ አቶ አሸናፊ ብርሃኑ ናቸው፡፡
አልኮል አብዝቶ ባለመጠቀም፣ ልቅ ከሆነ ግብረ ስጋ ግንኙነት በመታቀብና ለበሽታው አጋላጭ ከሆኑት ነገሮች እራስን በማቀብ ስርጭቱን ለመግታት የተያዘውን ዕቅድ ከግብ ለማድረስ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ አቶ አሸናፊ አሳስበዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ውብሸት ኃ/ማርያም – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ በሽታ ስርጭትን ለመግታት የተያዘውን ዕቅድ ከግብ ለማድረስ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ ጥሪ አቀረበ

More Stories
በከምባታ ዞን ሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርአት (E-LMIS) ምዝገባ በይፋ መጀመሩን የከተማው ኢንተርፕራይዝና ሥራ ዕድል ፈጠራ ጽህፈት ቤት አስታወቀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በተከሰተው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ተደረገ
ህብረተሰቡ የኤሌክትሪክ መስመሮችን ጨምሮ ለእሳት አደጋ መንስኤ የሚሆኑ የመጠቀሚያ ዕቃዎችን በጥንቃቄ በመጠቀም በሰው ህይወት እና ንብረት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት መከላከል እንደሚገባ ተገለጸ