የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ በሽታ ስርጭትን ለመግታት የተያዘውን ዕቅድ ከግብ ለማድረስ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ ጥሪ አቀረበ
የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ የኤች.አይ.ቪ/ኤድስና ጉበት በሽታ መከላከያና መቆጣጠር ዘርፍ አስተባባሪ አቶ ዳዊት ፈይሳ በህብረተሰቡ ዘንድ በተፈጠረው መዘናጋት የቫይረሱ ስርጭት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የበሽታው ስርጭት እየጨመረ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ዳዊት፤ ይህን ለመግታት የተያዘውን ዕቅድ ከግብ ለማድረስ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበቀዋል፡፡
በትምህርት ቤቶች፣ በሀይማኖት ተቋማት፣ በገበያ ስፍራዎችና በህዝብ መገኛ ስፍራዎች ስለበሽታው አስከፊነት ግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት በመስጠት የበሽታውን ስርጭት ለመቀነስ እየሠሩ መሆናቸውን የገለጹት በመምሪያው የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ በሽታ መከላከል ባለሙያ አቶ አሸናፊ ብርሃኑ ናቸው፡፡
አልኮል አብዝቶ ባለመጠቀም፣ ልቅ ከሆነ ግብረ ስጋ ግንኙነት በመታቀብና ለበሽታው አጋላጭ ከሆኑት ነገሮች እራስን በማቀብ ስርጭቱን ለመግታት የተያዘውን ዕቅድ ከግብ ለማድረስ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ አቶ አሸናፊ አሳስበዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ውብሸት ኃ/ማርያም – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ በሽታ ስርጭትን ለመግታት የተያዘውን ዕቅድ ከግብ ለማድረስ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ ጥሪ አቀረበ

More Stories
ለግብርናው እድገት መንግስት ከሚያደርገው ጥረት ጎን ለጎን የግብርና አጋር አካላት ድጋፍ የማይተካ ሚና እንዳለው የጎፋ ዞን ግብርና መምሪያ ገለጸ
በዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ የጥምቀት በዓል በተለያዩ ሀይማኖታዊ ክዋኔዎች በድምቀት ተከብሯል
የ1447ኛው ዓመተ ሂጅራ የሀጅ ምዝገባ ጥር 18 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ የሲዳማ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት አስታወቀ