የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ ዙር የከፍተኛና መካከለኛ የአመራሮች ስልጠና በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል መሰጠት ጀመረ
ስልጠናው “በመደመር መንግስት የዘርፎች እምርታ” በሚል መሪ ቃል የሚሰጥ ነው፡፡
በመደመር መንግስት እይታ የግብርና፣ የገጠር ትራንስፎርሜሽን፣ የኢንዱስትሪ ዘርፍ፣ የከተማ ልማት እንዲሁም የቱሪዝም ዘርፍ እመርታ በሚሉ ርዕሶች ስልጠናው የሚሰጥ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
በብልጽግና ፓርቲ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን የስልጠናውን መነሻ ሰነድ እያቀረቡ ይገኛሉ፡፡
በክልሉ የሚገኙ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች በቦንጋ ከተማ መሰጠት በጀመረው ስልጠና እየተሳተፉ ይገኛል፡፡
ዘጋቢ፡ ዳንኤል መኩሪያ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
በመንግስት ድጋፍና በህብረተሰቡ ተሣትፎ የተገነባው ጤና ጣቢያ በጎፋ ዞን ደንባ ጎፋ ወረዳ ወይዴ ውርኪ ማዕከል ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
የሳውላ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ወንጀልን የሚጸየፉ አምራች ዜጎችን ለማፍራት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገለፀ
በዳውሮ ዞን ገና ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የምረጡኝ ቅስቀሳና የፓርቲ ምርጫ ምልክት የማስተዋወቅ መርሃ ግብር ተካሄደ