የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ ዙር የከፍተኛና መካከለኛ የአመራሮች ስልጠና በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል መሰጠት ጀመረ
ስልጠናው “በመደመር መንግስት የዘርፎች እምርታ” በሚል መሪ ቃል የሚሰጥ ነው፡፡
በመደመር መንግስት እይታ የግብርና፣ የገጠር ትራንስፎርሜሽን፣ የኢንዱስትሪ ዘርፍ፣ የከተማ ልማት እንዲሁም የቱሪዝም ዘርፍ እመርታ በሚሉ ርዕሶች ስልጠናው የሚሰጥ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
በብልጽግና ፓርቲ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን የስልጠናውን መነሻ ሰነድ እያቀረቡ ይገኛሉ፡፡
በክልሉ የሚገኙ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች በቦንጋ ከተማ መሰጠት በጀመረው ስልጠና እየተሳተፉ ይገኛል፡፡
ዘጋቢ፡ ዳንኤል መኩሪያ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
የፊቼ ጫምባላላ በዓል በሀዋሳ ከተማ በሲዳማ ባሕል አዳራሽ በድምቀት እየተከበረ ይገኛል
በወራቤ ዩኒቨርስቲ ሴቶችን ወደ አመራርነትና ውሳኔ ሰጪነት ለማምጣት ባለፉት አመታት በተከናወኑ ስራዎች ለውጦች እየተመዘገቡ መምጣታቸው ተመላከተ
50ኛው የኢትዮጵያ ሴቶች ቀን (ማርች 8) በዋቸሞ ዩኒቨርስቲ እየተከበረ ነው።