የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ ዙር የከፍተኛና መካከለኛ የአመራሮች ስልጠና በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል መሰጠት ጀመረ
ስልጠናው “በመደመር መንግስት የዘርፎች እምርታ” በሚል መሪ ቃል የሚሰጥ ነው፡፡
በመደመር መንግስት እይታ የግብርና፣ የገጠር ትራንስፎርሜሽን፣ የኢንዱስትሪ ዘርፍ፣ የከተማ ልማት እንዲሁም የቱሪዝም ዘርፍ እመርታ በሚሉ ርዕሶች ስልጠናው የሚሰጥ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
በብልጽግና ፓርቲ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን የስልጠናውን መነሻ ሰነድ እያቀረቡ ይገኛሉ፡፡
በክልሉ የሚገኙ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች በቦንጋ ከተማ መሰጠት በጀመረው ስልጠና እየተሳተፉ ይገኛል፡፡
ዘጋቢ፡ ዳንኤል መኩሪያ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
የሕዝቡን አዳጊ የልማት ፍላጎት ለማሟላትና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት አዲስ ተሿሚዎች በትጋት ሊሠሩ እንደሚገባ በአሪ ዞን የደቡብ አሪ ወረዳ ምክር ቤት አባላት ገለፁ
የወጣቶችን የስራ ፈጠራ ክህሎት ማዳበርና የፋይናንስ አቅም ማጎልበት ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ ማንሰራራት ሚናው የላቀ መሆኑ ተገለጸ
የፖሊስ አባላት የኢትዮጵያን ክብርና ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ከመቼውም ጊዜ በላይ ሊሰሩ ይገባል – ርዕሰመስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)