‎በልማትና በመልካም አስተዳደር የሚነሱ ጥያቄዎች ለመመለስ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ ተገለጸ

‎በልማትና በመልካም አስተዳደር የሚነሱ ጥያቄዎች ለመመለስ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ ተገለጸ

‎ሀዋሳ፡ ሕዳር 09/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የህዝቡን የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ የጌዴኦ ዞን ምክር ቤት አባላት አስታወቁ።

‎ምክር ቤቱ ባካሄደው 4ኛ ዙር 13ኛ አስቸኳይ ጉባኤ የዞኑ አስተዳደር ያቀረበውን የተለያዩ ሹመቶች የምክር ቤቱ አባላት ተቀብለው በሙሉ ድምፅ አፅድቀዋል፡፡

‎የጌዴኦ ዞን አስተዳደሪ ዝናቡ ወልዴ(ዶ/ር) በጉባኤው ባስተላለፉት መልዕክት ለሕብረተሰቡ ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት አንድነትን በማጠናከር ለሁንተናዊ ዕድገት ከመቼውም ይልቅ በትጋት ሊንሠራ ይገባል ብለዋል፡፡

‎ዛሬ ሹመት ከተሰጣቸው መካከል አቶ ፀጋዬ ታደሰ የምክር ቤቱ ዋና አፌ ጉባኤ ሲሆኑ በተሰጣቸው ኃላፊነት በታማኝነትና በቅንነት የወከለውን ህዝብ ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

‎አሁን ያለንበት ወቅት እንደ ዞን የቡና ምርት የሚሰበሰብበት በመሆኑ ህብረተሰቡም ያገኘውን ሀብት በመቆጠብ ኢኮኖሚውን ለማሳደግ የበኩሉን ጥረት እንዲያደርግ አፌ ጉባኤው መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

‎በጉባኤው የተሳተፉ የምክር ቤት አባላት በሰጡት አስተያየት አዲስ ሹመት ከተሰጣቸው አካላት ጋር በመቀናጀት በልማትና በመልካም አስተዳደር ዙሪያ ከህዝቡ የሚነሱ ጥያቄዎችን ለመመለስ ከወትሮው ይልቅ እንደሚሠሩ ገልፀዋል፡፡

‎የዞኑ አስተዳደሪ ዝናቡ ወልዴ(ዶ/ር) በጉባኤው የዞኑ ምክር ቤት ዋና አፌ ጉባኤን ጨምሮ የተለያዩ ሹመቶችን አቅርበው የምክር ቤቱ አባላት ገንቢ አስተያየት በመስጠት በሙሉ ድምፅ አፅድቀዋል፡፡

‎ዘጋቢ፡ ውብሸት ኃ/ማርያም – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን