የዞኑ ዋና አስተዳዳሪን ጨምሮ ከፍተኛ የሥራ አመራሮች የከፍተኛ ፍርድ ቤቱን የሥራ እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል፡፡
የስራ ከባቢን ምቹና የስራ ተነሻሽነት ከመፍጠር አኳያ ያለው አስተዋዕጾ በቀላሉ የሚገመት አለመሆኑን የተናገሩት የባስኬቶ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት አቶ ታጋይ ኩምሳ÷ የተጀመረው የለውጥ ሥራ ወደ ስር ፍ/ቤቶች እንዲሰፋ ይደረጋል ብለዋል።
የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የራሱ ህንፃ መኖሩ የሚያስመሠግን ነው ያሉት ፕሬዝደንቱ የዲጂታል ቴክኖሎጂ መሳሪያዎች እጥረት፣ የድምፅ መቅረጫ ማሽን ያለመኖርና፣ የተሽከርካር እጥረት ተቋሙ ይበልጥ አገልግሎቱን ቀልጣፋ እንዳያደርግ ማነቆ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
የፍርድ ቤቱን ደረጃ በማሻሻል ለማህበረሰቡ ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የተጀመሩ ውጥን ተግባራትን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባም የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ሳሙኤል ደሳለኝ ጠቁመው÷ ዞኑ በተነሱ ችግሮችና ቀጣይ ማስተካከያ በሚሹ ጉዳዮች ዙሪያ አቅም በፈቀደ ለማስተካከል ጥረት ያደርጋል ብለዋል።
ዘጋቢ: አወል ከድር – ከሳውላ ጣቢያ

More Stories
በመንግስት ድጋፍና በህብረተሰቡ ተሣትፎ የተገነባው ጤና ጣቢያ በጎፋ ዞን ደንባ ጎፋ ወረዳ ወይዴ ውርኪ ማዕከል ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
የሳውላ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ወንጀልን የሚጸየፉ አምራች ዜጎችን ለማፍራት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገለፀ
በዳውሮ ዞን ገና ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የምረጡኝ ቅስቀሳና የፓርቲ ምርጫ ምልክት የማስተዋወቅ መርሃ ግብር ተካሄደ