የዞኑ ዋና አስተዳዳሪን ጨምሮ ከፍተኛ የሥራ አመራሮች የከፍተኛ ፍርድ ቤቱን የሥራ እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል፡፡
የስራ ከባቢን ምቹና የስራ ተነሻሽነት ከመፍጠር አኳያ ያለው አስተዋዕጾ በቀላሉ የሚገመት አለመሆኑን የተናገሩት የባስኬቶ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት አቶ ታጋይ ኩምሳ÷ የተጀመረው የለውጥ ሥራ ወደ ስር ፍ/ቤቶች እንዲሰፋ ይደረጋል ብለዋል።
የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የራሱ ህንፃ መኖሩ የሚያስመሠግን ነው ያሉት ፕሬዝደንቱ የዲጂታል ቴክኖሎጂ መሳሪያዎች እጥረት፣ የድምፅ መቅረጫ ማሽን ያለመኖርና፣ የተሽከርካር እጥረት ተቋሙ ይበልጥ አገልግሎቱን ቀልጣፋ እንዳያደርግ ማነቆ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
የፍርድ ቤቱን ደረጃ በማሻሻል ለማህበረሰቡ ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የተጀመሩ ውጥን ተግባራትን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባም የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ሳሙኤል ደሳለኝ ጠቁመው÷ ዞኑ በተነሱ ችግሮችና ቀጣይ ማስተካከያ በሚሹ ጉዳዮች ዙሪያ አቅም በፈቀደ ለማስተካከል ጥረት ያደርጋል ብለዋል።
ዘጋቢ: አወል ከድር – ከሳውላ ጣቢያ

More Stories
ለትምህርት ሥራ ስኬታማነት ባለድርሻ አካላት በቁርጠኝነትና በጋራ መስራት እንዳለባቸው ተገለፀ
በበጀት አመቱ በ71 ሺህ 219 መዛግብት ላይ ውሳኔ መስጠት መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ማህበረሰብ ባህላዊ እሴቶች ሳይበረዙ ለትውልድ ለማስተላለፍ የኪነ ጥበብ ዘርፉን በማጠናከር ላይ እንደሚገኝ የጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ አስታወቀ