ብልጽግናን ለማረጋገጥ የፖሊስ አመራር እና አባላትን አቅም ማሳደግ ይገባል – ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
ሀዋሳ፣ ህዳር 08/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) ብልጽግና ለማረጋገጥ የፖሊስ አመራር እና አባላትን አቅም ማሳደግ ይገባል ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ተናገሩ፡፡
ከጆኦስትራቴጂ ኩስምና ወደ ታደሰ ቁመና በሚል መሪ ሀሳብ ለክልሉ የፖሊስ አመራሮች እና አባላት ስልጠና በወላይታ ሶዶ ከተማ እየተሰጠ ይገኛል ።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ እንደገለፁት ኢትዮጵያ ለመላው አፍሪካ ሀገራት የስልጣኔ ተምሳሌት የነበረችና በጦርነት ወቅትም ሌሎች ሀገራትን የምታግዝ፤ ሌሎች ነፃ የወጡበትን ቀን ሲያከብሩ ኢትዮጵያ ግን የድል ቀኗን የምታከብር ሀገር ናት።
ስትራቴጂክ አቅማችን የሚመዘነው ከምንም በላይ በሰራነው ልማትና ባስመዘገብነው ድል በመሆኑ የውስጥና የውጪ ጠላትን በመመከት እና ያሉ ፀጋዎችን በመጠቀም የኢትዮጵያን ከፍታ እናረጋግጣለን ብለዋል።
የሀሳብ ኩስምና ከነበረበት ሰርቶ የሚያሰራ መሪ በመኖሩ ትልልቅ ፕሮጀክቶች መጀመራቸው እንኳን ሳይታወቅ የሚጠናቀቁበት ጊዜ ላይ እንደምትገኝ ገልፀዋል።
ለኩስምና ካበቁን ፈተናዎች ውስጥ ከነጠላ ትርክቶች በተጨማሪ የመዋቅር መዳከም እና የመሳሉት ምክንያት በመሆናቸው ሁለንተናዊ ሪፎርም በማድረግ ተቋማትን የማጠናከር ስራ መስራቱን ገልፀዋል።
ከስልጠናው ማግስት የፖሊስ አባሉ ቁመናውን በማደስ ሰላም ወዳዱን ማህበረሰብ በመጠቀም አካባቢውን ከወንጀል ስጋት ነፃ ማድረግ ይገባልም ብለዋል።
ዘጋቢ ፦ገነት መኮንን-ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
ባለፉት ዘጠኝ ወራት 5.5 ቢሊየን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች በተለያዩ ዘርፎች ወደስራ መግባታቸውን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልሉ ንግድና ኢንቨስትመንት ቢሮ አስታወቀ
በዳዉሮ ዞን እየተሠሩ የሚገኙ የልማት ሥራዎች ለህዝቡ የመልማት ጥያቄ ምላሽ እያስገኙ መሆናቸዉ ትኩረት ሊደረግባቸው እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ
በዘመናዊ የእንስሳት እርባታ ዘርፍ በመሰማራታቸው የቤት ፍጆታን ከማሟላት ባሻገር በኢኮኖሚ ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን በጋሞ ዞን ገረሴ ከተማ በዘርፉ የተሰማሩ አንዳንድ አካላት አረጋገጡ