ህዳር 29 ለሚከበረው የ20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በዓል የአሰልጣኞች ሥልጠናና ማስፈፀሚያ ዕቅድ ላይ የውይይት መድረክ በካራት ከተማ እየተካሄ ይገኛል
20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን “ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኀብረ ብሔራዊ መግባባት” በሚል መሪ ሀሳብ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ካራት ከተማ የአሰልጣኞች ሥልጠናና ማስፈፀሚያ ዕቅድ ላይ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው።
በውይይቱ ላይ የ20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በዓል አከባበር ዕቅድ ይቀርባል።
በመቀጠልም “ዲሞክራሲያዊ የፌደራል ስርዓት በኢትዮጵያ” የሚል ሰነድ የህገ-መንግስት ትርጉም እና አስተምህሮ ዳይሬክቶሬት ተቀዳሚ ዳይሬክተር አቶ ሉቃስ ጅማ ቀርቦ ውይይት ይደረግበታል ተብሎ ይጠበቃል።
በመድረኩ የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አዳማ ትንጳዬ፣ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲን ጨምሮ የሁሉም ዞኖች፣ አፈ ጉባኤዎች፣ የኮሙኒኬሽ ኃላፊዎች፣ የደቡብ ሬድዮና ቴሌቪዥን ድርጅት አርባ ምንጭ ቅርንጫፍ ስራ አስክያጅ፣ የሴቶችና ወጣቶች ክንፍ እዲሁም ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች እና ተጋባዥ እንግዶች ይሳተፋሉ።
ዘጋቢ፡ ተዋበች ዳዲ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን
ህዳር 29 ለሚከበረው የ20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በዓል የአሰልጣኞች ሥልጠናና ማስፈፀሚያ ዕቅድ ላይ የውይይት መድረክ በካራት ከተማ እየተካሄ ይገኛል

More Stories
ባለፉት ዘጠኝ ወራት 5.5 ቢሊየን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች በተለያዩ ዘርፎች ወደስራ መግባታቸውን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልሉ ንግድና ኢንቨስትመንት ቢሮ አስታወቀ
በዳዉሮ ዞን እየተሠሩ የሚገኙ የልማት ሥራዎች ለህዝቡ የመልማት ጥያቄ ምላሽ እያስገኙ መሆናቸዉ ትኩረት ሊደረግባቸው እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ
በዘመናዊ የእንስሳት እርባታ ዘርፍ በመሰማራታቸው የቤት ፍጆታን ከማሟላት ባሻገር በኢኮኖሚ ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን በጋሞ ዞን ገረሴ ከተማ በዘርፉ የተሰማሩ አንዳንድ አካላት አረጋገጡ