በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን ምሁር-አክሊል ወረዳ በመንግስትና በህብረተሰቡ የተከናወኑ የተለያዩ የልማት ሥራዎች የምረቃ ሥነ-ሥርዓት እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ሕዳር 06/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን ምሁር-አክሊል ወረዳ በመንግስትና በህብረተሰቡ የተከናወኑ የተለያዩ የልማት ሥራዎች የፌደራል፣ የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራሮችና የሥራ ኃላፊዎች፣ የሀይማኖት አባቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት የምረቃ ሥነ-ሥርዓት እየተካሄደ ይገኛል።
አምባሳደር ምስጋናው አረጋ በጎ አድራጎት ድርጅት በ26 ሚሊዮን በጀት ያስገነባቸው የሐዋሪያት የመጀመሪያ ደረጃና መካከለኛ ትምህርት ቤት እና በ20 ሚሊየን ብር ወጪ የሐዋሪያት ወደ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የተሸጋገረው ልማት ሥራዎች ይጠቀሳሉ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶ/ር እዮብ ተካልኝ፣ አምባሳደር ምሰጋናዉ አረጋ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ቢሮ ኃላፊ አቶ አሰፋ ደቸ፣ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ ጨምሮ የተለያዩ የሀገር ዉስጥና የዉጪ እንግዶች በምረቃዉ ሥነ-ሥርዓት ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ተስፋዬ ወ/ማሪያም

More Stories
ባለፉት ዘጠኝ ወራት 5.5 ቢሊየን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች በተለያዩ ዘርፎች ወደስራ መግባታቸውን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልሉ ንግድና ኢንቨስትመንት ቢሮ አስታወቀ
በዳዉሮ ዞን እየተሠሩ የሚገኙ የልማት ሥራዎች ለህዝቡ የመልማት ጥያቄ ምላሽ እያስገኙ መሆናቸዉ ትኩረት ሊደረግባቸው እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ
በዘመናዊ የእንስሳት እርባታ ዘርፍ በመሰማራታቸው የቤት ፍጆታን ከማሟላት ባሻገር በኢኮኖሚ ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን በጋሞ ዞን ገረሴ ከተማ በዘርፉ የተሰማሩ አንዳንድ አካላት አረጋገጡ